Quantcast
Channel: admin – Medrek
Viewing all 3686 articles
Browse latest View live

አዲስ አበባን ያካተተ ሸዋ የሚባል ክልል አስፈላጊነት (ክፍል 3) – ግርማ ካሳ

$
0
0

ከጥቅት ወራት በፊት በጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር ከፍተኛ አመራር አባል፣ ኦቦ ቃሲም ሁሴን አባናሻ፣ ላስ ቬጋስ በሚገኝ የሕሊና ራዲዮ ጣቢያ ላይ ቀረቡ። “ኦሮሞው የራሱን እድል በራሱ የመወሰን መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል። ይሄ እኮ ዴሞክራሲያዉ የሆነ አለም አቀፍ መርህ ነው። ለምንድን ነው ሰዎች ህዝብ ድምጽ ይስጥ ሲባል የሚቃወሙት ?” አሉ። እርሳቸው ድምጽ ይስጥ የሚሉት ኦሮሚያ ውስጥ ያለውን ህዝብ ነው። ያለ ህዝብ ፍቃድ፣ በሃይል የተመሰረተች አንዲት ክልል ዉስጥ የሚኖሩ የአንድ ብሄረሰብ ተወላጆች ብቻ የሚሰጡትን ድምጽ፣ በየትኛው የህግ መስፈርትና ሚዛን ተቀባይነት ሊኖረው እንደሚችል ግልጽ ባይሆንም፣ የኦነጉ አመራር ኦሮሞው ድምጽ ሰጥቶ መገንጠል ፍላጎቱ ከሆነ ኦሮሚያን የመገንጠል መብቱ መረጋገጥ እንዳለበት ተከራክረዋል። (ያው የተለመደዉና የከሸፈበት የአርባ አመታት የኦነግ አቋም)

ኦቦ ቃሲም ተያያዥ ጥያቄ ቀረበላቸው። “እሺ የኦሮም ህዝብ ድምጽ የመስጠትና የፈለገውን የመምረጥ መብት አለው ካልን፣ ለምሳሌ በብዛት አማርኛ ተናጋሪና ከተለያዩ ብሄረሰቦች የሆነው የአዳማና የምስራቅ ሸዋ ህዝብ፣ በኦሮሚያ ዉስጥ መቀጠል አንፈለግም ቢል የህዝቡ ራስን በራስ የመወሰን መብት ተከብሮለት፣ ከኦሮሚያ መውጣት ይችላል ወይ ? “ ብለው ተጠየቁ። የኦቦ ቃሲም ትክክለኛ መልስ መለሱ።”በሚገባ፤ ይችላሉ” ነበር ያሉት።

አዲስ አበባ ወደ ሰባት ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ ሊኖርባት እንደሚችል ይገመታል። የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ መዲና ከመሆኗም በተጨማሪ የአገሪቷ የኢኮኖሚክ ማእከልም ናት። አዲስ አበባ የሁሉም ናት። ለስራ፣ ለመሻሻል ከሁሉም የአገሪቷ ክፍሎች ሰው ወደ አዲስ አበባ ይጎርፋል። የተቀረው የኢትዮጵያ ግዛት በዘር በመከፋፈሉ ዜጎች በሁሉም የአገሪቷ ግዛት በነጻነት የመኖር፣ የመመላለስ እድላቸው በጣም የጠበበ ሆኗል። “ይሄ የናንተ መሬት አይደለም» ተብለው በሚናገሩት ቋንቋ ምክንያት፣ በተለይም አማራ ተብለው ዜጎች እንዲፈናቀሉ ተደርጓል። የሥራ እድል የሚነፈጉበት ሁኔታም ነው ያለው። ስለዚህ ሰላም ፣ ደህንነት የሚፈልግ ፣ ለሕልዉናው ሲል አቅጣጫዉን ወደ አዲስ አበባ ያዞራል። አዲስ አበባ መሸሸጊያና መጠለያ ስለሆነች። በናቴ በኩል እጅግ በጣም ብዙ ዘመዶች ነበሩኝ። ሃረር አካባቢ። አሁን ብዙዎቹ ወደ አዲስ አበባ መጥተዋል።

አዲስ አበባ ከመስፋቷ የተነሳ፣ አዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ከተሞችም፣ በጣም አድገዋል። አዳማ/ናዝሬት በአንድ ሰዓት ይገባል። ቢሾፍቱ፣ ሰበታና ቡራዮ የአዲስ አበባ አካል ናቸው ማለት ይቻላል። ቡራዩ በሕዝብ ብዛት ከአምቦ በልጣለች። ሰበታ ከወሊሶ በልጣለች። ቢሾፍቱ ከነቀምቴ በልጣለች። አዳማን ጨምሮ በዚያ የሚኖሩ ዜጎች የስነ-ልቦና አመለካከታቸው አዲስ አበባ ካሉት ጋር የተመሳሰለ ነው። የናዝሬት ልጅ ሲባል የአዲስ አበባ ልጅ እንደማለት ነው። በአጭሩ አዲስ አበባና አካባቢዋ (አዳማን ጨመሮ) በኢኮኖሚና በማህበረሰባዊው ረገድ ተሳስረዋል። አሁን ያለው ሕወሃትና ኦህዴድ በሃይል የዘረጉት የፖለቲካ አርቴፊሻል መስመሮችና ግንቦች ናቸው። አዲስ አበባ ማንም ዜጋ፣ ዘር. ሃይማኖት ሳይጠየቅ በነጻነት ይኖራል። አርቴፊሻሉን የፖለቲካ መስመር አልፎ ኦሮሚያ ሲገባ ግን የተለየ ታሪክ ነው። የፈጠጠ ዘረኝነትን እናያለን። በባለስልጣናቱ።

እንግዲህ እኛ እየጠየቅን ያለነው በአዲስ አበባና አካባቢዋ ያለው ህዝብ (አዳማን ጨመሮ) የራሱን እድል በራሱ ይወስን የሚል ነው። ሳይፈለግ አፋን ኦሮሞ ብቻ የሥራ ቋንቋ በሆነባት፣ የአፓርታይድ አይነት አንድን ዘር ብቻ የመጥቀም መንግስታዊ አሰራር በሰፈነባትና ከ25 አመት በፊት በተፈጠረችዋ ኦሮሚያ መቀጥል ካልፈለገ ሕዝቡ ከኦሮሚያ ክልል የመውጣት መብቱ ሊክበርለት ይገባል።

አንዳንድ ወገኖች ይሄ ከሆነ ደም መፋሰስ ነው ይላሉ። ሊያስፈርሩን ይሞክራሉ። ይሄን አይነት ማስፈራራትን በማየት አንዳን ደካማ ድርጅቶች ለነዚህ ወገኖች ማስፈራሪያ የተንበረከኩም አሉ። “እነርሱን ማቀፍ አለብን” እያሉ ሊለማመጧቸው ይሞክራሉ። እንዴት ነው ከአሁን ለአሁን ወለጋና አርሲ ያሉ ወጣቶች ያምጻሉና ተብሎ አዲስ አበባን ጨመሮ የሸዋ ህዝብ ባልፈለገው አስተዳደር፣ ባልፈለገው ክልል መቀጠል አለበት የሚባለው? እንዴት ነው ከሁን ለአሁን አርሲ የተወለዱት እነ ጃዋር፣ ወለጋ የተወለዱት እነ ሌንጮ ለታ ይቃወማሉና እኛ አዲስ አበባና ናዝሬት የተወለድን ያለፍላጎታችን፣ በአገራችን እንደ እንግዳና መጤ የምንቆጠረው ? ይህ በሕግም ፣ በሞራልም፣ በዴሞክራሲም አንጻር አያስኬድም።

ለዚህ ነው አማርኛና አፋን ኦሮሞ የሥራ ቋንቋ የሆነበት፣ ሁሉም በ እኩልንት የሚተዳደሩበት፣ አዲስ አበባን ጨመሮ ሸዋ የሚባል ክልል ይኖር ብለን የምንከራከረው። ይሄን በማለታችን አንዳንድ ወገኖች በኦሮሞው ላይ እንደመነሳት፣ የኦሮሞዉን ገበሬ እንደመበደል፣ፌዴራሊዝምን እንዳለመቀበልና የድሮው ስር፤ዓት እንደመናፈቅ አድርገው ዉይይቱን አቅጣጫ ሊያስቀይሩ ይሞክራሉ።

1. አፋን ኦሮሞ ከዓምርኛጋር የሥራ ቋንቋ ይሆናል። ያ ማለት ሁለት ወይም ሶስት የአፋን ኦሮሞ ትምህት ቤቶች ማቋቋም ስይህን 9አሁን ኦሮሞው አክቲቪስቶች እንደሚጠይቁት) በሁሉም የአዲስ አበባ፣ በአማራው ክልል የሰሜን ሽዋ ዞን ሳይቀር አፋን ኦሮሞ እንደ ትምህርት ይሰጣል። አፋን ኦሮሞ አድማሱን ያሰፋል። ታዲያ ይሄ እንዴት ጸረ-ኦሮሞ ሊሆን ይችላል”

2. በድሮው ስርዓት የሥራ ቋንቋው አማርኛ ብቻ ነበር። አሁን አፋን ኦሮሞም የሥራ ቋንቋ ይሆናል። ያ ማለት በኢሕአዴግ መንግስት ተገኘ የተባለው በቋንቋ የመገልገል፣ የመማር መብት አይወሰድም። የሚሆነው አንዱ ወይ ሌላው ከማለት አማርኛም አፋን ኦሮሞም ሁለቱም የሥራ ቋንቋ ይሆናሉ። በድሮው ስርዓት አሃድዊ ስርአት ነው የነበረው። አሁን የፌዴራል ስርዓት ነው የሚሆነው። ልዩነቱ ግን አዲስ አበባና አካባቢ ወይም ሸዋ የራሱ አንድ ፌዴራል ክልል ይሆናል።

በአዲስ አበባና በአካባቢዋ በተለይም በከተሞች ብዙ ከተለያዩ ብሄረሰቦች የተወለዱ አማርኛ ተናጋሪዎች በብዛት እንዳሉት፣ በገጠራማ አካባቢዎች የሞሉት የኦሮሞ ገበሬዎች ናቸው። ይህ የኦሮሞ ማህብረሰብ በአፋን ኦሮሞ የሚገባውን አገልግሎት ያገኛል። ልጆቹ አፋን ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን አማርኛም ይማሩለታል። ይናገሩለታል። በቀላሉ ኢኮኖሚው ውስጥ ይገቡለታል። በነጻነት ገበሬው ያመረተውን አዲስ አበባ ቢሾፍቱ፣ አዳማ…. ሄዶ መሸጥ ይችላል። አዲስ አበባ ያለው የልማት፣ የጤና፣ የትምህርት እንቅስቃሴ ተካፋይ ይሆናል።

3. የኦሮሞ ገበሬዎች ከመሬታቸው በልማት ስም እየተፈናቀሉ የግፍና የሰቆቃ ሰለባ መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው። ግን ሸዋ የሚባል ክልል መኖሩ የገበሬውን ችግር አያባብስም። ኦሮሚያ የሚባል ክልል መኖሩ የገበሬውን ችግር እንዳልቀነሰ። ላለፉት 25 አመታት የኦሮሞ ገበሬ የተፈናቀለው ኦሮሚያ በምትባል ክልል ውስጥ እየኖረ ነው። ( የኦሮሞ ገበሬ ችግር መሰረቱና ምንጩ የመሬት ፖሊሲው ነው። አዲስ አበባ አካባቢ ያሉ መሬቶች ዋጋቸው ትልቅ ስለሆነ መሬቱን ሸጦ ብዙ ትርፍ ሊያገኝበት ሲችል ያ ሊሆን አልቻለም። ሊያገኝ ከሚገባው ትርፍ ከአዲስ አበባ ራቅ ብሎ በፊት ነበረው መሬት ሶስት፣ ራት እጥፍ የሚሆን መሬት ሊገዛበት ይችል ነበር። አሁን ባለው ሁኔታ ግን መሬት የመንግስት ስለሚባል፣ ገዢዎች ለገበሬው እንበል 10 ሺህ ብር ሰጥተው፣ በልማት ስም ያፈናቅሉትና ለኢንቨስተሮች መቶ እጥፍ ያከራዩታል። ዘጠኝ ሚሊዮን ዘጠኛ ሺህ ኪሳቸው ያስገባሉ ማለት ነው። መሬት የገበሬው ከሆነ ግን ፣ ገበሬው ምን አልባት አሥር በመቶ ግብር ቢከፍል እንጂ አብዛኝው ግንዘብ ኪሱ ነው የሚገባው። )

የገበሬው መሰረታዊ ጥያቄ የሰላም፣ የመብት፣ የፍትህና የልማት ጥያቄ ነው። አፋን ኦሮሞና አማርኛ የሥራ ቋንቋ የሆነበት፣ አዲስ አበባን ጨምሮ ሸዋ የሚባል ክልል ከኖረ፣ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ እያሉ መከፋፈሉ ቀርቶ፣ ሁሉም በስራዉና በዜግነቱ ተከብሮ ፣ የአንዱ ቅርስ የሌላው፣ የአንዱ ቋንቋ የሌላው ሆን፣ አገራችንን በፍቅርና በአንድነት የምናሳድግበት አጋጣሚ ይፈጥርልናል።

አንዳንዶች ስለሸዋ የጻፍከው ለሁሉም አገሪቷ የሚሰራ ነው ይላሉ። በከፊል ትክክል ናቸው። እንድ ጂማ፣ አሰላ አካባቢ ያሉ ከአዲስ አበባ አካባቢ ግር ተመሳሳይነት አላቸው። ግን ደግሞ ወደ ምእራብ ወለጋ ዞኖች ብትሄዱ በዚያ 97% አፋን ኦሮሞ ተናጋሪዎች ባሉበት ቦታ አማርኛም የሥራ ቋንቋ ይሁን ማለት ብዙ አያስኬድም። ሸዋ ግን የተለየ ነው። አዲስ አበብባ ጨመሮ ከግማሽ በላይ አፋን ኦሮሞ ተናጋሪ አይደለም።

The post አዲስ አበባን ያካተተ ሸዋ የሚባል ክልል አስፈላጊነት (ክፍል 3) – ግርማ ካሳ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


የእኔ ጀግኖች፤ ሦስቱ ዘመነዎች – ሙሉቀን ተስፋው

$
0
0

በልዩ ልዩ አጋጣሚ የተለያየ ስምና ግብር ካላቸው ዕልፍ ሰዎች ጋር ተዋውቄያለሁ፤ በሕይወት መስተጋብር እንደሌላው ሰው ሁሉ፡፡
‹‹ዘመነ›› የሚባል ስም ያላቸው ሦስት የተለያዩ ሰዎችን አውቃለሁ፤ ሦስቱም ከተራራ የገዘፈ ታሪክና የታላቅ ስብዕና ባለቤቶች ናቸው፡፡ ከስሙ ይሁን ወይም አጋጣሚው የማውቃቸው ‹‹ዘመነዎች›› እንዲህ ናቸው፤ የእኔ ‹‹ዘመነዎች›› ዘመነ ካሤ፣ ዘመነ ምሕረትና ዘመነ ጌጤ ይባላሉ፡፡
የሕዝባቸው ብሶት ከማንም በላይ የገባቸው ናቸው፤ ከፊታቸው ከቀረበላቸው ሹመትና ሽልማት ይልቅ የዘመዶቻቸውን የመከራ ቀንበር መሸከም የመረጡ፣ የአንድ ትውልድ ፈርጦች! ስንት ሰው ነው ከፊቱ ያለውን ደስታና ፍስሃ ተጸይፎ ራሱን በመከራ ውስጥ ለሚገኝ የመንፈስ ደስታ የሚያጭ? እንዲህ ያለ ስብዕና መላበስ ዝም ብሎ አይገኝም፡፡ አርቆ ማሰብን፣ ማሰላሰልን፣ የሕዝብን ብሶት መስማትና ማዬት ከስጋዊ ጊዜያዊ ደስታ ይልቅ መንፈሳዊ ወኔን ይጠይቃል፤ ያኔ ነው ከፍ ወዳለ የላቀ ሰውነት የሚታደገው፡፡ ሦስቱም ዘመነዎች ይኼው ነው መገለጫቸው፤ በዚህ ሰዐት እነዚህ ዘመነዎች ለእኛ መኖር ራሳቸውን አደጋ ላይ የጣሉ ናቸው፡፡
ዘመነ ካሤ ከፊቱ በላይ በላዩ የሚመጣለትን ሹመትና ሽልማት እየተቀበለ ስጋውን በድሎት ሸፍኖ የውስጡን ጥያቄ እያፈነ ቢቆይ ኖሮ አሁን እንደመቀ መኮንን ከደረሱበት ቦታ ላይ መገኘት ለእርሱ ምንም አልነበረም፡፡ ግን ከግብዝነት ይልቅ ሰውነትን መረጠ፤ በናቡከደነፆር ቤት ከሚገኘው የቤተ መንግሥት እልፍኝ ድግስ ይልቅ ቆሎ መቆርጠም በቂ ነው አለ፤ የያዘውን ሹመት አየው- ተጸየፈው፡፡ የባሕር ዳር ያማሩ ዝምባባዎች፣ የጣና ሐይቅ ነፋስ፣ የሜጫ ማርና ወተት፣ የቆጋ መስኖ እሸት ዘመነን ወደ ኋላ እንዲመለስ አላደረጉትም፡፡ ሹምብጥ ያለው የተንጣለለ ቢሮው ኦና እንደሆነ በኅሊናው ተመለከተው፤ ኦና በሆነ ቢሮ ሊቀመጥ የሚችል ሰው የሆነ ሰው እንደማይኖር ሲገነዘብ ጊዜ አልፈጀበትም፡፡
ዘመነ ምሕረት በዩንቨርሲቲ ታሪክ አጥንቷል፤ በወያኔዎች ሹመት መጣለት- አስተማሪ ሆኖ ለተማሪዎቹ ታሪክን በተግባር ማስተማር እንዳለበት ወሰነ፡፡ ከታላላቅ ከተማዎች ይልቅ በበለሳና በደምቢያ ገጠራማ አካባቢዎች ተተኪዎችን ታሪክ አስተማረ፤ በቃል ሳይሆን በተግባር፡፡ ዘመነ ምሕረትን ታሪክ ምንድን ነው? ብሎ የሚጠይቅ ተማሪ የሚኖር አይመስለኝም፤ ለምን ቢባል ዘመነ ታሪክን እየሠራ ነውና የሚያሳያቸው፡፡ ከአቶ ማሙሸት አማረ ጋር በመሆን መኢአድን በመላው ኢትዮጵያ አቀጣጠሉት፡፡ በምርጫ 2007 ጊዜ ዘመነ እንዲህ አለ ‹‹ወያኔ ከሚባል ሌባ ኮሮጆ ጥበቃ አንቀመጥም፤ ለራሱ ሲል አያጭበርብር አሊያ ግን እንኳንስ እናቴ ሞታ እንዴውም አልቅስ አልቅስ ይለኛል›› ነው ያለው፡፡ ዘመነ ብዙ ጊዜ ሲናገር ሰምቼዋለሁ፤ ያኔ ያደረገው ታሪካዊ ንግግር ግን አፍ የሚያስከፍት ነበር፡፡ ዘመነ ተናግሮ ዝም የሚል ሰው አይደለም፤ ቃል መጠበቅና መታመን ከዘመነ በላይ ማን ይኖራል? አቤት ለዓላማ ያለው ጽናት! በዐማራነቱ ያልደረሰበት ችግር የለም፤ ግን አይበገርም፡፡ ከሕጻን ልጁ ፊት በመሣሪያ አፈሙዝ ተደብድቧል፤ በጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ ዐይኑ ተሸፍኖ ሰካራም ትግሬዎች ተጸዳድተውበታል! እርሱ ግን በዚህ ሁሉ መካከል ሆኖ ስለሚበድሉት ሰዎች ከስብዕና በታች ስለመሆናቸው ያዝናል! ወደ ልዕለ ስብዕና መጠጋት እንዲህ ነው፡፡ ዘመነ የግድያ አዋጅ ወጥቶበት አገዛዙ በበለሳ፣ አርማጭሆ፣ ቋራና ወገራ ከአምስት ጊዜ በላይ እርሱን ለመግደል ጋንታ ጦር ልኳል፤ ከዚህ ሁሉ ግን በጀብደኝት አምልጧል፤ ብዙ በጣም ብዙ… አሁን ግን አደጋ ላይ ነው (በዝርዝር እመጣበታለሁ ሌላ ጊዜ)፡፡ ዘመነ ለዐማራ ሕዝብ የመከራ መስቀል መሸከም የማያደክመው ፍጥረት!
ዘመነ ጌጤም ከላይኞቹ ከሁለቱ ዘመነዎች የተለየ አይደለም፡፡ በተማረበት ትምህርት ተቀጥሮ መሥራት ወይም የወያኔ ሹመኛ መሆን ለእርሱ ምንም ናቸው፡፡ ጥሩ መሥሪያ ቤት መቀጠርም ሹመኛ መሆንም ሁሉም በየተራ ግብዣ መጥተውለት ነበር፤ ሁሉንም ናቃቸው፡፡ ለእርሱ ሕይወት የዐማራ ሕዝብ የገጠመውን ሰቆቃ አሽቀንጥሮ መጣል ነው፡፡ ለዚህም ከመኢአድ ጓዶች ጋር ተሰለፈ፡፡ አገዛዙ መኢአድን አፈረሰው፡፡ ዘመነ ለዐማራ ሕዝብ መብቱን እንዲያስከብር በሰላማዊ መንገድ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የወጣትነት እድሜውን ሰውቷል፡፡ ባለፈው የካቲት ወያኔዎች ጎንደር ላይ ከክንዱ ዱቤ ጋር አፍነው ወሰዷቸው – ትግሬዎች ወደ ማዕከላዊ፡፡ ይኼው ከየካቲት ጀምሮ በማዕከላዊ በስቅይት ላይ ነው- ዘመነ ጌጤ፡፡
እኔ የማውቃቸው ዘመነዎች እንደዚህ ያሉ ጀግኖች ናቸው፡፡ ነገሩ የስማቸው ትርጓሜ በራሱ የተሻለ እሳቤን የሚሻ ነው፤ ዘመነ- ሰለጠነ፣ መጠቀ፡፡ እነዚህ ጀግኖች የመጠቁት በቁሳዊ ሀብት አይደለም፤ በአስተሳሰብ ነው፡፡ ለሕዝብ መስዋት መሆን መዘመን ነው፡፡
የዐማራ ሕዝብ ትግል አሸናፊ ነው የምለው እንደነ ዘመነዎች ያሉ ጀግኖችን ስለማይ ነው፡፡

The post የእኔ ጀግኖች፤ ሦስቱ ዘመነዎች – ሙሉቀን ተስፋው appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

አዲስ ነገር የለም ትግራይ የጉግማንጉጎች ምድር ከሆነ ሰነበተ – መስቀሉ አየለ

$
0
0
ከሶስት አመት በፊት በመዋዕለ ህማማት ወደ መቀሌ የተጓዘ አንድ በቅርብ የማውቀው ሰው በድፍን መቀሌ የጾም ምግብ የሚባል ነገር አጥቶ ምን ያህል እንደተቸገረ ገልጾልኝ ነበር።አጠር ባለ አማርኛ ሃጢያት ቤተመንግስቱን ባነጸባት የዘመናችን ሰዶምና ገሞራ ላስቬጋስ እያለሁ ያን ያህል በጾም ምግብ ማጣት አልተፈተንኩም። ቢያንስ ለቬጋን የሚባል የቅንጡዎች የአመጋገብ ዘይቤ አላቸውና በዛ በኩል እሸጎጥ ነበር ብሎኛል። ከሁሉ የገረመው የጾም ምግብ ማጣቱ አይደለም። ሰዎቹ በምሳ ሰዓት ከመሃል አገር እየተጫነ የሚመጣ ሰንጋ በሬ ቁርጥ ለመብላት በየሆቴል ቤቱ ተክተልትለው የሚያሳዩት መንሰፍሰፍ ግብር ሊበሉ በነጋሪት አዋጅ የተጠሩ እንጅ በገንዘባቸው ገዝተው የሚጠቀሙ አይመስሉም ነበር፤ እንደታዛቢው አገላለጥ።
ሌላው አስገራሚ ነገር መቀሌ ውስጥ ያሉ ቤተክርስቲያኖች እንደ አውሮፓ ቤተመደሶች መጋዘንና ሲኒማ ቤት ለመሆን የቀራቸው የሃያና ቢበዛ ሰላሳ አመት ጉዳይ እንደሆነ ገብቶኝ እርሜን አውጥቸ ነው የመጣሁት ብሏል።ምክንያቱም እዚያ በቆየባቸው ሳምንታት ማታ ማታ ለመሳለም ጎራ ባለባቸ ቤተክርስቲያናት ሁሉ አውደምህረቶቹ በሰው ድርቅ ተመተው እንዳያቸውና የቀሩትም ተሳላሚዎች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ እድሜያቸው በአመዛኙ ከስልሳ በላይ የሆኑት አረጋውያን እንደሆኑ፤ እነሱ ደግሞ ከጥቂት አስርተ አመታት ቦሃላ ሲያልቁ ወይንም አልጋ መያዝ ሲጀምሩ አጸዶቹ ዳዋ እንደሚበቅልባቸው ለማወቅ ነቢዩ ኤርሚያንስ መሆን አይጠቅም ማለቱ ነው።
ትግሬዎች ዛሬ እግዚአብሔርም ሆነ የሞራል ህግ አያስፈልጋቸውም። የነሱ የቃልኪዳን ዶሴ የደደቢቱ ማኔፈስቶ ነው። እንደፈለጉ እንዲዘርፉም እንዲገድሉም ከንብረት ባሻገር በነፍስና በስጋ ላይ ያልተገደበ ስልጣን የሰጣቸው ህወሃት መሆኑ ብቻ አደለም፤ አንድ ሰው ማንነቱን የምታውቀው በተጣላኸው ግዜ ነው እንዲሉ ለአምላኩ ያለውን ትህትና እና የአምልኮ ደረጃም የሚታወቀው እንዲሁ በችጋር ወቅት ሳይሆን በጥጋቡ ወራት ነው። ይኽ ሩብ ምእተ አመት ደግሞ ያሳየው ነገር ቢኖር ግን እኒህ መናፍሰት ነገሮች የወንጌልን የሞራል ህግ ቀርቶ በጣም ቀላል የሚባል ሰብአዊነትን ለመሸከም የማይቻላቸው የነተቡ መጽጉዎች መሆናቸውን ነው።የስርዓቱ ዘዋሪዎች እኮ እንደ ቁቤ ትውልድ በሽተኞች ሃይማኖቱን “ሃላፊነቱ የተወሰነ የነፍጠኛው የግል ኩባንያ” አድርገው እንደፈረጁት በየቤተ ሃይማኖቱ የሚሰሩትን ግፍ አጥርቶ መመልከት ነው:: ዛሬ በትግራይ ምድር ሃይማኖት ተረት ነው የምንለውም ለዚሁ ነው።የዘንዶውም እራስ ቢንሆ ባንድ ወቅት “እኔ የማምነው በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ነው” ብሎ ቃለ መጠይቅ መስጠቱን እናስታውሳለን። በርግጥም ሉሲፈራውያን (ምዕራባወያን) ሃያ አምስት አመት ሙሉ ክንዳቸውን የገተሩላቸው ዝም ብለው አይደለም። መድሃኒዓለም እንደተናገረ ሰይጣን ሰይጣንን አያወጣውም፤ አይኑን ገልጦ ላየ አፈሩን ፍም እሳት ያደረገላቸው መሳጢ ተኩላው አባ ጳውሎስ ቢሆኑ ከስብሃት ነጋና ከሳሞራ የማያንሱ ጉግማንጉግ እንደነበሩ ኑሯቸውም ብቻ ሳይሆን አሟሟታቸውም ያሳየው ነገር ነበር።
ዛሬም ቢሆን ደግሞ መቀሌ ያለ የአባይ ወልዱ ዘለፈቶ ቀርቶ አዲስ አበባ መንበረ ጵጵስናው ላይ የወጡት ፓትሪያሪክ በእግዚአብሔር ለማመናቸው ማረጋገጫ የለኝም። ቢያንስ ያለትውፊቱና ያለቀኖናው እስኪፈሰክ አላስችላቸው ብሎ በአብይ ጾሙ ወቅት ሱብኤውን አቃለው ከበሮ መትተው የተሾሙ ቀን በቅቶኛል። ዛሬ አንድ አይጠ መጎጥ አዲግራት ውስጥ ሂጃብ እንጅ ነጠላ መልበስ አይቻልም ብሎ ጅሃድ ሲያውጅ እንዲሁ ከባዶ ተነስቶ አይደለም። እድሜ ቢሰጣቸው ደግሞ ከሰማይ በታች የማይሞክሩት ክፋትና ግፍ እንደማይኖር እርግጠኛ ነኝ። ነገ ጀንበር ስትወጣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቋንቋ ጥናት ኢንስቲትዩት የነዚህ ጉዶች ሴራ ብቻ የያዘ እራሱን የቻለ “ሴራ-ፒዲያ ዘብሄረ ትግራይ ” አዘጋጅቶ ለዓለም እንደሚያበረክት ተስፋ ማድረግ ሞኝነት አይደለም።ቦ ግዜ ለኩሉ ነውና።

The post አዲስ ነገር የለም ትግራይ የጉግማንጉጎች ምድር ከሆነ ሰነበተ – መስቀሉ አየለ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

UK issues travel alert in Ethiopia

$
0
0

Summary


Download map (PDF)

The Foreign and Commonwealth Office (FCO) advise against all travel to:

  • within 10 km of the border with Eritrea, with the exception of the main road through Axum and Adigrat, and tourist sites close to the road (e.g. Debre Damo and Yeha)
  • areas off the principal roads/towns within 10 km of the borders with Sudan and Kenya
  • within 10 km of the border with South Sudan
  • the Nogob (previously Fik), Jarar (previously Degehabur), Shabelle (previously Gode), Korahe and Dollo (previously Warder) zones of the Somali region.
  • within 100 km of the Ethiopian border with Somalia and Kenya in the Afder and Liben zones of Ethiopia’s Somali region
  • the four woredas (districts) (Akobo, Wantawo, Jikawo and Lare) of the Nuer zone and the Jore woreda of the Agnuak zone of the Gambella region

The FCO advise against all but essential travel to:

  • the woredas (districts) of Tsegede, Mirab Armacho and Tach Armacho in North Gonder
  • Jijiga town in the Somali region
  • three woredas (districts) of the Agnuak zone of the Gambella region that border on South Sudan (Dima, Goge and Etang) and the Gambella wildlife reserve

Internet services, disconnected on 30 May 2017, have now been restored. However internet and other mobile data services can be restricted without notice, hampering the British Embassy’s ability to assist you. You should have alternative communication plans in place when travelling in Ethiopia. If you’re in Ethiopia and you urgently need help (eg if you’ve been attacked, arrested or there has been a death), call +251 (0)11 617 0100. If you’re in the UK and concerned about a British national in Ethiopia, call 020 7008 1500.

Demonstrations and violent clashes took place in the Oromia and Amhara regions in 2016. The situation has calmed considerably, but protests may occur with little warning and could turn violent. You should monitor local media, avoid large crowds, remain vigilant at all times and follow the advice of the local authorities and your tour operator.

There are local media reports of a possible hand grenade attack on 25 April 2017 at the Du Chateau Hotel in Gondar Town. This reportedly resulted in 5 people being injured, including a foreign national.

On 1 April 2017, there was an explosion at the Florida International Hotel in Gondar, reportedly the result of a grenade attack. Three people are reported to have been injured. Two separate explosions at hotels in Gondar and Bahir Dar occurred in January 2017. You should remain vigilant and follow the advice of the local authorities and your tour operator.

On 9 October 2016 the Ethiopian government declared a state of emergency. This announcement followed months of unrest in the Amhara and Oromia regions. On 30 March 2017, a four-month extension was approved, meaning the state of emergency is due to last until 8 August.

The Ethiopian government issued a public statement (unofficial translation) outlining the measures in place under the state of emergency. Failure to comply with these measures could lead to detention and/or arrest.

Restrictions on the movement of diplomats beyond Addis Ababa were lifted on 8 November 2016. On 15 March 2017, three further restrictions were lifted, including provision for curfews, arrests without court orders and some media restrictions.

Terrorists are likely to try to carry out attacks in Ethiopia. Attacks could be indiscriminate, including in places visited by foreigners.

You should be vigilant at all times, especially in crowded areas and public places like transport hubs, hotels, restaurants, bars and places of worship and during major gatherings like religious or sporting events. There is a threat of kidnapping in Ethiopia’s Somali region, particularly in the eastern areas to which the FCO advise against all travel. See Terrorism

The Ethiopia-Eritrea border remains closed. Several security incidents have taken place along the border. The risk of cross-border tensions remains. There is a threat of kidnapping along the border. See Local travel

Owning ivory is strictly prohibited in Ethiopia. Anyone caught in possession of ivory can expect to be detained by police. See Local laws and customs

Around 20,000 British nationals visit Ethiopia every year. Most visits are trouble free.

If you’re abroad and you need emergency help from the UK government, contact the nearest British embassy, consulate or high commission.

The Overseas Business Risk service offers information and advice for British companies operating overseas on how to manage political, economic, and business security-related risks.

Take out comprehensive travel and medical insurance before you travel.

The post UK issues travel alert in Ethiopia appeared first on Satenaw: Ethiopian News|Breaking News: Your right to know!.

ገዢው ኢሕአዲግ እና 16 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በድርድር አጀንዳዎች ላይ መነጋገር ጀምረዋል

$
0
0

ቅድመ ድርድሩ ከተጀመረ ወዲህ ታዛቢዎች ሲገኙ የዛሬው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

የቅድመ ድርድሩ ከተጀመረ ወዲህ ታዛቢዎች ሲገኙ የዛሬው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ገዥው ፓርቲ ኢሕአዲግ ለድርድር ፍቃደኛ የሆነባቸውና እንደዚሁም የማይቀበላቸው ርዕሶች ዛሬ ይፋ መደረግ ጀምረዋል። በምርጫ ሕጉ ላይ ለመነጋገር መፍቀዱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ ግን መነጋገር እንደማይቻል ማመልከቱ ከሚጠቀሱት መካከል ናቸው።

The post ገዢው ኢሕአዲግ እና 16 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በድርድር አጀንዳዎች ላይ መነጋገር ጀምረዋል appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

ጎንደር በጦር ሰራዊት ተወራለች! – ልያ ፋንታ

$
0
0

ጎንደር በሰራዊት መወረሯን የሰማ ጎንደር የተወለደ በስደት የሚገኝ ሁሉ እንቅልፍ አጥቷል። በህዝባችን ላይ የሚወርደው ስቃይ እና በደል በየትኛውም ክልል ከተማ የላቀ መሆኑ ከምሽቱ 12 ስአት ጄምሮ ኳስ ለመጫዎት ድንገት የወጣ ወጣት ቤቱ በር ላይ መታወቂያ የለህም ተብሎ ባደገበት ሰፈር፣ በወላጆቹ ፊት እየተደበደበ ወደ እስር ቤት ይገባል። እኛ ጎንደሬዎች ትግርኛን ከትግራይ ከሚመጡ የትግራይ ሰዎች በመስማት ስለለመድነው እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የወዳጂ፣ የወገን ቋንቋ ይመስለን ነበር ። አሁን ግን ደብዳቢዎቹ፣ ገራፊዎቹ፣ ገዳዮቹ የሚጠቀሙበት የአንባገነኖች ቋንቋ መሰለን። ( መሰለን ነው ያልኩ)
ከትግራይ ወጥተው ተው ! ይሄ ግፍ ደግም አይደል የሚሉ፣ ሞታችን ከጎንደር ግፍ ተቀባይ ህዝብ ጋር ያድርገው የሚሉ ጥቂት የማይባሉ በጎንደር እድሜ ልካቼውን ነዋሪ እነ አደይ ሒዎቷን መጥላት ጎንደሬውን ይከብደዋል። እኛ ጎንደሬዎች በዘር ላይ የተመሰረተም ጥላቻ አናራምድም። እያሳደዱ እየገደሉት ይቅር ማለትን ከሚያውቅ ህዝብ የተወለድን ያደግን ነን እና።
በጎንደር ባህል የተማረከ እና የታሰረ እስረኛን መደብደብ ነውርርር የሚባል ግፍ ነው። ዛሬ ለነጻነት ትግል ልጂሽ ወደ ትግል ሄዷል የተባለች እናት ጎንደር ላይ ትደበደባለች። ቁጥራቼው በሽህዎች የሆኑ ያለ ጠያቂ ማዕከላዊ ገብተው የሚሰቃዩትን ተውት ።
ግን ጎንደር ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ካርታ ለመፋቅ በታለመ እቅድ በጦር ስትወረር ምነው ሌላው ኢትዮጵያዊ እንዲህ ዝምም፣ ጭጭ አለ?
አበባዮ ጎንደር ፣ ከአንች ጋር ይሁን እግዚአብሔር!
ጨረስኩ ለዛሬው!
ልያ ፋንታ

The post ጎንደር በጦር ሰራዊት ተወራለች! – ልያ ፋንታ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሃውልት ሙሉ በሙሉ ፈረሰ

$
0
0

ኢሳት (ሰኔ 7 ፥ 2009)

የታዋቂው የህክምና ባለሙያ፣ የመአህድ መስራችና ፕሬዚደንት የነበሩት የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሃውልት ሙሉ በሙሉ ፈረሰ።

አፅማቸው ወዴት እንደሚወሰድ የታወቀ ነገር የለም። የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሃፊ አቡነ ሳዊሮስ ስለጉዳዩ እንደማያውቁ ለኢሳት ገልጸዋል።

ከሳምንታት በፊት የመካነ መቃብሩን አጥር በማፍረስ የተጀመረው እንቅስቃሴ ማክሰኞ ሰኔ 6 ፥ 2009 ሙሉ በሙሉ ሃውልቱን በማፍረስ ተጠናቋል። ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ፣ አጽማቸው ከመካነ መቃብር ያልወጣ ሲሆን፣ በቅርፅ የተሰራው ሃውልትም የተወሰደበት አልታወቀም።

የፕ/ር አስራት ወልደየስ ሃውልትን መፍረስ ከሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን አንዱ አቶ ሽመልስ ለገሰ ሁኔታውን በቁጣ ገልጸውታል።

ሃውልቱ ለምን እንደፈረሰ አልታወቀም። ሃውልቱን ለማፍረስ በደብሩ ሃላፊዎችም ሆነ በቤተ-ክህነት የተሰጠ ምክንያትም የለም።

የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት መስራችና ፕሬዚደንት ፕ/ር አስራት ወልደየስ፣ በደብረብርሃን ከተማ አማሮችን ለአመጽ አነሳስተዋል የሚል ክስን ጨምሮ በርካታ ወንጀሎች ተዘርዝሮባቸው አመታትን በወህኒ አሳልፈው መሞታቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቡነ ሳዊሮስ ሃውልቱ ለምን እንደፈረሰ ከኢሳት ለቀረበላቸው ጥያቄ የሚያውቁት ነገር አለመኖሩን ገልጸዋል። ጉዳዩ የሚመለከተው ጠቅላይ ቤተክህነትን ነው በማለት ጥያቄውን ወደዚያ መርተዋል።

ሃውልቱ ለምን እንደፈረሰ ተወሰነ የሚለውን ለማጣራት ኢሳት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት እንዲሁም ወደ ባለወልድ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ያደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

ታዋቂው የህክምና ባለሙያና ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ በህክምና ሙያቸው እጅግ የተከበሩ ባለሙያ የነበሩ ሲሆን፣ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት (መአህድ)ን በመመስረት በህወሃት ኢህአዴግ የስልጣን ዘመን በአማሮች ላይ የተነጣጠረውን ጥቃት ለመመከት በመንቀሳቀሳቸውም ለረጅም ዓመታት በወህኒ ማሳለፋቸው ይታወቃል።

በቀድሞ ከርቸሌ ወህኒ ቤት ውስጥ በነበሩት ወቅት በገጠማቸው ከፍተኛ የጤና ችግር የውጭ ሃገር ህክምና እንዲያገኙ የተደረጉ ተማፅኖዎች በመንግስት በኩል ተቀባይነት ባለማግኘቱ ጤናቸው በከፍተኛ ሁኔታ ካሽቆለቆለ በኋላ ከሃገር እንዲወጡ ቢፈቅድም፣ ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም።

ፕ/ር አስራት ወልደየስ በ70 አመታቸው በአሜሪካ ፔንሲልቪኒያ ግዛት ፊላዴልፊያ ከተማ ግንቦት 6 ቀን 1991 ህይወታቸው አልፏል። የቀብራቸው ስነስርዓትም በትውልድ ሃገራቸው ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ከተማ ባለወልድ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። በቀብራቸው ስፍራ ላይ ለመታሰቢያ የቆመውም ሃውልድ ከ18 አመታት በኋላ እንዲፈርስ የተደረገ ሲሆን፣ አጽማቸው ወዴት እንደሚወሰድም አልታወቀም።

The post የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሃውልት ሙሉ በሙሉ ፈረሰ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

ህወሃት በስሜንና ደቡብ ጎንደር ሕዝብ ላይ ጦርነት ለያካሂድ ዝግጅቱን አጠናቋል!! – አንተነህ ገብርየ”

$
0
0

አገር መራሹ የትግራይ ወንበዴ ቡድን ለአርባ ሦስት ዓመታት ያህል አማራውን እና የትግራይን ሕዝብ ደም ሲያፋሥስ ቆይቶ  የትግራይን ሕዝብ አሁንም ከሰው በላውና ፋሽስቱ ቡድን ጐን እንዲሰለፍ እየተማፀነ ፀረ-ሕዝብ ፕሮፓጋንዳውን እያናፈሰ እንደሚገኝ ከዚያው ከሀገር ቤት የምናገኛቸው መረጃዎች ይገልፃሉ።የትግራይ ሕዝብ ከዚህ ቀደም የፈፀመውን ስህተት ላለመድገምና ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አብሮ ለመኖር የሚያስችለውን ሁኔታ መፍጠር ያለበት አሁን ይመስለኛል።ይህ መሆን ካልቻለ የትግራይ ምድርም ሆነ በየትኛውም ምድር የሚኖር ትግሬ ቀን እንደሚጨልምበት ሊያውቅ ይገባዋል።ምክንያቶቹን በዝርዝር መግለጽ የሚያስፈልግም አይደለም ለምን ቢባል በአይን የሚታዩ በተግባር እየተፈፀሙ ያሉ ፋሽስታዊ ተግባሮች በመሆናቸው።ጊዜው አሁን ነው አሁን መሪዎቹ የሚያራግቡትን ፀረ-ሕዝብ ቅስቀሳ ማክሸፍና ክንዱን በራሱ በህወሃት ላይ ማንሳትና ህወሃትን ለማስወገድ መታገል ይኖርበታል።ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን ለሚደርሰው ማንኛውም የሰውና የንብረት ኪሳራ ተጠያቂው ራሱ የትግራይ ሕዝብና ድርጅቱ ህወሃት እንደሚሆኑ ሊታወቅ ይገባዋል።ለምን ቢባል የትግራይ ሕዝብ ህወሃትን ተቀብሎ ከማስተናገዱ በፊት ሰከን ብሎ ማሰብና ከድርጅቱ በስተጀርባ ማን አለ?ድርጅቱ የሚታገልለት ዓላማ ለማን ይጠቅማል?በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ሊያስከትል የሚችለው ምንድን ነው?አሁንስ ይህ እኩይ ድርጅት እየፈፀመ ያለው ምንድን ነው?የሚል አንድም ነገር ተነስቶ አልሰማንም አላየንም ከዚህ ከፍ ብሎ ከዚህ በኋላ ለሚሆነው ነገር ሁሉ ተጠያቂዎች ህወሃትና የትግራይ ሕዝብ ብቻና ብቻ ትሆናላችሁ ያልኩት ለዚህ ነው።

የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ እንዲሉ መገንጠል አለብን ብሎ የተገነጠለው ሻእብያና የኤርትራ ሕዝብም ከተገነጠሉ በኋላ በህወሃት እግር እየታከኩ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሀብት መመዝበርና በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ ስለሆኑ ህወሃትን ከመደገፍ አልፎ መተባበርና በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ በተለይም በአማራው ሕዝብ ላይ የሰነዘሩትን የጥፋት እጃቸውን በአስቸኳይ ሊያነሱ ይገባቸዋል።ካልሆነ ግን እላይ ለመጠቆም የሞከርኩት እነሱንም የአጠቃለለ ሊሆን እንደሚችል ሊገባቸው ይገባል።በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት የስንቶቹ አካል እንደጎደለ፤የሰው ሕይወት እንደጠቀጭና የሀገር ሀብት እንደወደመ የቅርብ ትውስታችንና ቁስላችንም ስለሆነ በፍፁም የምንረሳው ጉዳይ አይሆንም።ማን ተጠቃሚ እንደሆነም እየተመለክትን ነው ያም ሆኖ ደግሞ ለእልቂቱ ምክንያት የሆነው ጉዳይ እልባት ሳያገኝ እንደተንከረፈፈ ይገኛል ለምን እንደዚህ ሆነ?ቢባል የአዲስ አበባዎቹ ኤርትራውያንና የአስመራዎቹ ትግራይዋን ከጌቶቻቸው ትእዛዝ ጠብቀው የሰው ቁጥር ለመቀነስ ባልገመትነውና ባልጠበቅነው ሰአት እሣቱን እንደሚለኩሱት አንባቢዎቸ ልብ እንድትሉልኝ እጠይቃለሁ።ሌላው መጠቀስ ያለበት ጉዳይ ያኔ የጦርነቱ ጊዜ ኤርትራውያን በጣት የሚቆጠሩት ካልሆኑ በስተቀር አብዛኛዎቹ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በገፍ ታፍሰው በጭነት መኪና ወደ ኤርትራ መጓዛቸው ይታወቃል።

አሁን ላይ ያለውን ሁኔታ ስንመለከት ደግሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፤መለስተኛ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲትዎች በኤርትራውያን ተማሪዎች ተጨናንቀው እንደሚገኙ ግልጽ ነው፤ቤት የተወረሰባቸው እየተመለሰላቸው ነው ከዚህ ስንነሳ ቀደም ሲል ታምራት ኤርትራ ሄዶ በተፈራረመው ውል መሠረት የአሰብ ወደብ ኢንሹራን፤የመንገድ ጥገና፤የመንግሥት ሠራተኞች የነበሩ ኤርትራውያን የጡረታ ክፍያ፤የንግድ እንቅስቃሴና ሌሎች ተቋማት በሙሉ ይመለሳሉ፤ኤርትራውያ ወደ ውጭ ሀገር ሲወጡ የሚጠቀሙበት ቪዛ የኢትዮጵያ ነው ጠቅለል አድርጎ ለማስቀመጥ ታምራት የተፈራረመባቸውን ውሎች አሁን ፈልጌ ባላገኛቸውም ብዛታቸው 25 ነጥቦችን ያካተተ እንደነበር አስታውሳለሁ ታዲያ እነዚህ ሁሉ ውሎች ለኢትዮጵያ አንዳችም ፋይዳ እንደአልነበራቸውና ኤርትራውያንን ለመጥቀም ሲባል የተፈፀመ ደባ ወይም ታሪካዊ ውንብድናና ክህደት ነበር።ኤርትራ ደርግ ከወደቀ በኋላ ለመቋቋሚያ ድጎማ ያገኘችው ከኢትዮጵያ ነው አውሮፕላኖች የተወሰዱትም ደርግ ከወደቀ በኋላ ነው ወደ 80ሽህ የሚጠጉ ምስኪኖች ጦርነት ውስጥ ተማግደው በእግረኛና በአየር በከባድ መሣርያና በጥይት አረር የተቆሉበት ጦርነት ውጤት ከንቱ ሆኖ ሲቀር ምናልባትም በኢትዮጵያ በኩል በ10ሽዎች የሚቆጠሩ ምርኮኞች መንግሥት የሌላቸው በመሆኑ ዛሬም በእሥራት ላይ ይገኛሉ።

ነገሩ ከላይ ከላይ ያጎርሳታል እንዲሉ ሆነና እሥር ላይ ያሉት የሚያስፈታቸው አጥተው የነገው ተስፈኞች ደግሞ ለነፃመት እንታገላለን በሚል ሽፋን ኤርትራ ገብተው በማንቧረቅ ብዙዎቹን ለእስራትና ሌሎች ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዲዳረጉ ለማድረግ ሌት ተቀን ተግተው እየሰሩ ይገኛሉ።ከጅማሮው ኤርትራ ገብቸ ታግየ ኢትዮጵያን ነፃ ላወጣ ነው የሚለው ቀልድ ነው ለምን ቢባል ከዚህ ያደረሰንን ችግር ዘውር ብሎ መፈተሽ ያሻል የኢትዮጵያ ጉዳይ  ሲነሳ እንደሚያቅለሸልሻቸው የግንቦት ሰባት መሪዎች ኢሳያስ አፈወርቂ ደግሞ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ሲነሳ አይኑን ጎልጉሎ ለጥፋት እንደሚነሳ ግልጽ ነው እነ አያ ነዓምን ዘለቀም ይህን ኮርጀው እየተጠቀሙባት እንደሆነ ይታወቃል።ይህ ሁሉ ውጣ ውረድ እንድምታው ሲታይ አማራውን ኢላማ ውስጥ አስገብቶ ከፊትና ከኋላ በመሆን ዘሩን ማጥፋት እንደሆነ ማጠንጠኛው መታወቅ አለበት።አንዳንዶቹ በሬ ካራጁ የሆኑ ግራ የተጋቡ አማራዎች ግንቦት ሰባት ኤርትራ መግባቱ ልክ አይደለም ተብሎ ሲተች ደማቸው የሚጨምርና ታዲያ በየት ገብተው ይታገሉ ብለው የሚሟገቱ ብዙ ናቸው ታግሎ ውጤት ካልተገኘ ምን ፋይዳ አለው?ሲታሰብ ቢውል ሻእብያ ህወሃትን ውጉ ብሎ ከኤርትራ ጦር ይሰዳል ብሎ ማሰብ ከመጃጃልም በላይ ነው።

ይህን ሁሉ መንደርደርያ እንድጽፍ ያደረገኝ ምክንያት ተስፋፊውና ፍሽስቱ ህወሃት በ1972ዓ/ም ክረምት ላይ ተከዜን በመከራ ከተሻገረ በኋላ ሌታና ቀን የጥፋት እጁን የሠነዘረው በስሜን ጎንደር በተለይም በወልቃይት፤ጥገዴ፤ ጠለምትና አርማጭሆ ሕዝብ ላይ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን።ከ1972ዓ/ም ጀምሮ ምን ያህል ሕዝብ ተገድሏል?ከቦታው ተፈናቅሏል፤ሀብት ንብረቱን ተዘርፏል የሚለውን በየድረገጹና በመጻሕፍት ተደጋግሞ የተገለፀ ስለሆነ ወደዚያ አልገባም።ይህ ሁሉ ሲሆን የእነዚያ አካባቢ ነዋሪዎች እጅ እግራቸውን አጣጥፈው ይመለከቱ ነበር ማለት አይደለም።በተናጠል በቡድን የጠላትን ኃይል መከላከልና መምታት ነበረበት የተደራጀ ባለመሆኑና በተለይም በውጭ ሰዎች የሚደረግ መገፋፋት ስለነበረበት አመርቂ ውጤት ማምጣት አልቻለም ነበር።የወልቃይትንና ጠገዴን ሕዝብ ጥያቄ ይዘው ሕገ-መንግሥቱ በሚፈቅደው መንገድ ሄደን የአማራ ማንነታችንን እናረጋግጣለን ብለው የተነሱ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ሌሎች ወንድሞቻችን ጉዳዩን ይፋ ካደረጉት በኋላ በርከት ባሉ አካባቢዎች ጉዳዩ የሕዝብን ትኩረት ሊስብ ቻለ።ወራሪ የህወሃት ቡድን ብዙ የአቅጣጫ ማስቀየሻ ዘዴዎችን ተጠቀመ/አማራና ቅማንት በማለት ያለ አግባብ የወገኖቻችንን ደም አፋሰሰ ግን በሕዝብ ተሳትፎ ነገሩ ቶሎ ብሎ ተቋጨ/፤በኃይል ለማንበርከክ ሞከረ የራሱን ኃይል እያስመታ እንዲያፈገፍግ ተገደደ።የዛሬ ዓመት ገደማ የአማራ ማንነት ጉዳይ አስፈፃሚዎችን የአማራ ክልል ተብየዎች ሳያሳውቁና ሳይናገሩ ተመሳሳይ ዩኒፎርም በማልበስ የአማራ ልዩ ኃይል አስመስሎ አፋኝ ወደ ጎንደር ከተማ አስገብቶ አፈና ተጀመረ 4የሚሆኑት የመታፈን አጋጣሚ ሲደርስባቸው 5ኛው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ለማፈን የሄዱት በጨለማ እጅህን ስጥ ሲሉት እኔ በጨለማ እጀን አልሰጥም ሲል ጥቃት ሰንዝረው ቤቱን በቦንብ መትተው ሊገድሉት ሲሞክሩ የአልሞት ባይ ተጋዳይ ሆኖ ራሱን እየከላከለ እንዳለ የጎንደር ከተማና የአካባቢው ሕዝብ ፈጥኖ በመድረስ ከታፈነው እንዲወጣ ሲደረግ ሌሎች የሕይወት መሰእዋትነት ከፍለዋል እሱም ብዙ ሳይቆይ ወህኒ ቤት ገብቶ ዛሬ በሕሊና እስረኝነት ላይ ይገኛል።ያች የሐምሌ 5/2008ዓ/ም ጎንደር ላይ የፈነዳች ጥይት ምን እንዳስከተለች አገር ያወቀው ጉዳይ ነው።እንግዲህ ጅራፍ ራሷ ገርፋ ራሷ ትጮሃለች ሆነና ነገሩ ወራሪውና ተስፋፊው የህወሃት ቡድን ለምለም ሣርና መሬት ባየ ቁጥር ማራቁን ማዝረብረቡ የተለመደ ስለሆነ እኛ ስለወልቃይትና ጠገዴ ጠለምትና አርማጭሆ ጉዳይ እያወራን እነሱ ጠቅላላውን ሰሜን ጎንደርን መውሰድ አለብን በማለት በስሜንና ደቡብ ጎንደር ሕዝብ ላይ በየወሩ የጦርነት አዋጅ ያውጃሉ አሁን ደግሞ ያለ የሌለ ኃይላቸውን በመሳብ ወደ ጎንደር በማከማቸት ላይ እንዳሉ ይህንም ገዱ አንዳርጋቸው ታማኝ ባለመሆኑ አዲሱ ለገሰና በረከት ስምኦ እያማከሉ እንዲመሩትና የአማራውን የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ለማሳለጥ ወደ ባህር ዳር በመሄድ የእልቂቱ ፊታውራሪዎች ተብለው ተሰይመዋል።

“”ስለዚህ አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ””በሚለው ብሂል የአማራ ሕዝብ ወንዝ ተራራ ሳይገድብህ በጎንደር እንዲቀጣጠል የተፈለገውን ሕዝብ የሚጨርስ የጦርነት አዋጅ በተባበረ ክንድ ለመመከት መዘጋጀት አስፈላጊ ነው ጊዜ መውሰድና ድርጊቱን አቅልሎ መመልከት በፍጹም መታሰብ የለበትም።በተለይ ከላይ የጠቀስኳቸው ሁለት ጅቦች ከኢህአፓ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የአማራውን ሕዝብ እያስፈጁ የዘለቁና ሎሌነታቸውን ያስመሰከሩ ፀረ-አማራ ግለሰቦች ህወሃት ባህርዳር ላይ ወስዶ ማስቀመጡ የሰውን ስም በነቂስ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ስለሚያውቁት ግጭቱ ከተከሰተ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ግምት ውስጥ በማስገባት እያንዳንዱን የሚሰነዘር ጥቃት በጥበብ ለመመከት እንዲቻል ይታሰበበት።እያልኩ በውጭ የምንኖር አማራዎችና የአማራ ወገን የሆናችሁ በሙሉ ከሕዝቡ ጎን በመቆም የሚቻለውን ድጋፍና ትብብር እንዳንነፍገው እያልኩ ወገናዊ ጥሬየን አስተላልፋለሁ።

 

  • አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!!!።

“ አንተነህ ገብርየ”

The post ህወሃት በስሜንና ደቡብ ጎንደር ሕዝብ ላይ ጦርነት ለያካሂድ ዝግጅቱን አጠናቋል!! – አንተነህ ገብርየ” appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


“የአፋን ኦሮሞ ፊደል /ቁቤ/ ቅደም ተከተል አልተለወጠም” -የአሜሪካ ኢምባሲ ባለሥልጣን

$
0
0

“የአፋን ኦሮሞ ፊደል /ቁቤ/ ቅደም ተከተል ተለውጧል መባሉ እውነት አይደለም” ሲሉ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ ባለሥልጣን ተናገሩ፡፡

በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የማስተማሪያ ቋንቋዎች ፊደላትም፣ በነበራቸው ቅደም ተከተል እንዲቀጥሉ ድጋፋችንን አንሰጣለን አሉ፡፡ በኤምባሲው የኢንፎርሜሽን ክፍል ኃላፊ ኒኮላስ ባርኔት ይህንን የተናገሩት በቅርቡ በርካታ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ላይ የሕፃናትን ንባብ ለማሻሻል በተካሄደ ጥናት የአፋን ኦሮሞ ፊደላት ወይም ቁቤ ቅደም ተከተል ተቀይሯል የሚለውን ውዝግብ ተከትሎ ነው።   ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፈይል ያድምጡ።

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/06/4810aa29-0437-4d55-afe2-259f938fb8ca_32k.mp3″});

The post “የአፋን ኦሮሞ ፊደል /ቁቤ/ ቅደም ተከተል አልተለወጠም” -የአሜሪካ ኢምባሲ ባለሥልጣን appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

ESAT Daily News Wed 14 Jun 2017

በጉራጌ ዞን የዐማሮች ንብረት ወደመ፤ በሕግ ጥበቃ ስር ያለ ዐማራ በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፎ ተገድሏል – ሙሉቀን ተስፋው

$
0
0

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ግምቱ ከአምስት ሚሊዮን ብር የሆነ የዐማራ ተወላጆች ንብረት ከሰኔ 4 እስከ ሰኔ 6 ቀን 2009 ዓ.ም በቀቤና ብሔረሰብ አባላት መውደሙን ከቦታው ዛሬ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል፡፡ አንድ በሕግ ከለላ ሥር ያለ የዐማራ ተወላጅ ወጣትም ተቀጥቅጦ ተገድሏል፡፡

መረጃውን ያደረሱን ሰዎች ጉዳዩ እንዴት እንደተጀመረ ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ እሁድ ሰኔ 4 ቀን አንዲት የቀቤና ተወላጅ እናት እና ለጊዜው ስሙ ባልታወቀ ሰው መካከል ጠብ ተነስቶ የሴቷ ሕይወት አለፈ፤ ሴቲዮዋን የገደለው ሰው መጥፋቱን ተከትሎ የቀቤና ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር ውድማ ጣሰው ወጣት መስፍን አዳነ ፀጋዬ የተባለን የዐማራ ተወላጅ በጥርጣሬ እኩለ ቀን ላይ እንዲታሰር አደረገ፡፡ እኩለ ሌሊት ሲሆን ተጠራርተው ለተሰባሰቡ የቀቤና ብሔረሰብ አባላት ጨፍጭፈው እንዲገድሉት በዕለቱ በጥበቃ ላይ የነበሩ የፖሊስ አባላት መስጠታቸው ተገልጧል፡፡
በዕለቱ በጥበቃ ላይ የነበሩት ፖሊሶች ኮንስታብል ገነት ንጋቱና ኢንስፔክተር ሀብታሙ ሲሆኑ በቀቤና ፖሊስ ጣቢያ የነበረውን ወጣት መስፍን አዳነ ሌሊት ላይ በስለት ሰውነቱ ተቆራርጦና በሕብረት ተጨፍጭፎ እንዲገደል አድርገዋል፡፡ የሟች አስከሬን በቀጣዩ ቀን ተለቃቅሞ እንደተቀበረም ለማወቅ ችለናል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ ከሰኞ ጀምሮ በወልቂጤ ከተማ በልዩ ልዩ ሥራ ተሰማርተው የሚኖሩ ዐማሮች ቤታቸው እየተመረጠ መቃጠሉንና መዘረፉ የታወቀ ሲሆን ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ወድሟል ተብሏል፡፡ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑት አብዛኛዎቹ ዐማሮች ባለፉት ዓመታት ከደቡብና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ምዕራብ የኖኖና አመያ ወረዳዎች ንብረታቸው ተቃጥሎ የሸሹ እንደሆኑ በተጨማሪ ገልጸውልናል፡፡ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ለዐማሮች ምንም ዓይነት የሕግ ከለላ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ችለናል፡፡

The post በጉራጌ ዞን የዐማሮች ንብረት ወደመ፤ በሕግ ጥበቃ ስር ያለ ዐማራ በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፎ ተገድሏል – ሙሉቀን ተስፋው appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

We Stop at Nothing – Walta Information Center – Walta Information Center (blog)

$
0
0

Over the past two years we have passed through monstrous events that require both the temperament and resilience of democratic citizens who are endowed with a cleaver insight of an intelligent politician. We managed to work unperturbed under the daunting influences of the changing circumstances that could even defy every intelligent the judgments of ours.


 


The ruling party has shown admirable sensibility and has also managed to display the composure of a seasoned political organization in handling the difficult matters that had pushed it into the tight-spots. Coping up with these soul-searching predicaments, it has tried to fully grasp the kernel of the matter that deeply concerns our nation and its people by way of scrutinizing its performances over the last 15 years and finally came-up with a suitable solution that would surly address the legitimate grievances of the public.


 


At any rate, we are still witnessing that Ethiopia is boldly journeying to democracy and prosperity and it has now reached at a place where it can see a bright light at the end of the tunnel – a tunnel dug by the iron fingers of poverty. This tunnel is blindingly dark and it can only be lighted with flames of an undefeatable spirit of a visionary leader who has the knack to dispel the intricacy of structurally embedded poverty that must again be combined with an indefatigable determination to tread on the arduous path of development.


 


And so far we have managed to register laudable economic success on continental and world scale. According to recently published 2017 United Nations World Investment Report, among African countries Ethiopia was by far the most dynamic and largest FDI recipient (accounting for almost half of the total inflows of LLDCs in Africa). This is an achievement mainly due to improvements in infrastructure and advances in industrialization sectors.


 


The same report has indicated that the FDI inflows rose for a fourth consecutive year in Ethiopia. The 2017 continued upward trend of FDI in has enabled it to stand among the top 5 recipient economies, which include Angola, Mozambique Bangladesh and Myanmar. Thanks to investments in infrastructure and manufacturing, Ethiopia again posted strong growth in FDI (up 46 per cent to $3 billion) and became the second largest LDC host economy, up from the fifth position in 2015.


 


Ethiopia attracted new FDI in manufacturing, which could create opportunities for local SMEs to link to global supply chains. Chinese investors have played a major role in other LDCs, such as Ethiopia, where they have focused on garment and leather production. Although China was one of the major sources of FDI, foreign investors from other economies have started investing more in Ethiopia’s agro-processing, hotels and resorts, as well as in its manufacturing activities.


 


In general, East Africa received $7.1 billion in FDI in 2016, 13 per cent more than in 2015. However, the aggregate increase masks divergent FDI performance within the sub-region. Flows to Ethiopia rose by 46 per cent to $3.2 billion, propelled by investments in infrastructure and manufacturing.


For instance, a $3.7 billion fertilizer plant project from Morocco signaled LDC’s, such as Ethiopia, potential to attract large-scale manufacturing projects in non-garment industries. Morocco’s Saham Finances for $375 million. Moroccan firms, the world’s largest phosphate exporter, signed at the end of 2016 a joint venture with Ethiopia to build a $3.7 billion fertilizer plant.


The government has also shown an unprecedented readiness to consolidate its democratic institutions. The government has vowed to support media practitioners and institutions operating without being defiant to professional ethics and compromising the rule of law. The media will be encouraged to seek, impart and disseminate information that would expose illicit actions and ensure accountability and good governance. The government has pledged to promote investigative journalism and guarantee the full implementation of the freedom of information Act.


Similarly, it has committed itself to dispel the preponderance of rent-seeking orientations and practices to ensure the supremacy of developmental political economy. The government also determined to dry-out the quagmire that would allow rent-seeking ideologies and tendencies to thrive. Redoubling effort in this regard would push aside the major obstacle in the journey to our renaissance.


Furthermore, the government resolved to strengthen the multi-party democracy. The ruling party has understood that excessive adversarial politics would tarnish and spoil the common mission of any political community. In fact, adversarial politics is said to create the right conditions for effective scrutiny of the government, and for genuine debate. However, when political adversaries are blindly engaged in an unbridled powers struggle driven by zero sum-game principle it would lead the democratic system to crisis. Thus, the party vowed to create platforms where it will have genuine consultation with opposition parties. Moreover, it also aimed to strengthen political participations citizens to promote deliberative democracy.


The government believes that the current rapid economic development will be sustained, accelerated and the inclusive double-digit growth is the fruit of the genuine democratic system put in place two decades ago. The need to deepen our democracy still exists and deepening our democracy is a serious matter that assumes a gravity of life and death. The government has committed itself to create a law abiding public service and officials who have the gut to uphold the public interest over and above their selfish agendas. The ruling party does not need spineless camp followers who would sell their political oath short.


Notwithstanding to the fact that we have cumbersome tasks to straighten the cultural setbacks and to unknot the meshes of backwardness, we have to take decisive steps in deepening our democracy and ensuring the sovereignty of our people through an ever increasing popular participation. We will continue to march on our developmental path and we will stop at nothing.


 


We Stop at Nothing – Walta Information Center (blog)

$
0
0

Over the past two years we have passed through monstrous events that require both the temperament and resilience of democratic citizens who are endowed with a cleaver insight of an intelligent politician. We managed to work unperturbed under the daunting influences of the changing circumstances that could even defy every intelligent the judgments of ours.


 


The ruling party has shown admirable sensibility and has also managed to display the composure of a seasoned political organization in handling the difficult matters that had pushed it into the tight-spots. Coping up with these soul-searching predicaments, it has tried to fully grasp the kernel of the matter that deeply concerns our nation and its people by way of scrutinizing its performances over the last 15 years and finally came-up with a suitable solution that would surly address the legitimate grievances of the public.


 


At any rate, we are still witnessing that Ethiopia is boldly journeying to democracy and prosperity and it has now reached at a place where it can see a bright light at the end of the tunnel – a tunnel dug by the iron fingers of poverty. This tunnel is blindingly dark and it can only be lighted with flames of an undefeatable spirit of a visionary leader who has the knack to dispel the intricacy of structurally embedded poverty that must again be combined with an indefatigable determination to tread on the arduous path of development.


 


And so far we have managed to register laudable economic success on continental and world scale. According to recently published 2017 United Nations World Investment Report, among African countries Ethiopia was by far the most dynamic and largest FDI recipient (accounting for almost half of the total inflows of LLDCs in Africa). This is an achievement mainly due to improvements in infrastructure and advances in industrialization sectors.


 


The same report has indicated that the FDI inflows rose for a fourth consecutive year in Ethiopia. The 2017 continued upward trend of FDI in has enabled it to stand among the top 5 recipient economies, which include Angola, Mozambique Bangladesh and Myanmar. Thanks to investments in infrastructure and manufacturing, Ethiopia again posted strong growth in FDI (up 46 per cent to $3 billion) and became the second largest LDC host economy, up from the fifth position in 2015.


 


Ethiopia attracted new FDI in manufacturing, which could create opportunities for local SMEs to link to global supply chains. Chinese investors have played a major role in other LDCs, such as Ethiopia, where they have focused on garment and leather production. Although China was one of the major sources of FDI, foreign investors from other economies have started investing more in Ethiopia’s agro-processing, hotels and resorts, as well as in its manufacturing activities.


 


In general, East Africa received $7.1 billion in FDI in 2016, 13 per cent more than in 2015. However, the aggregate increase masks divergent FDI performance within the sub-region. Flows to Ethiopia rose by 46 per cent to $3.2 billion, propelled by investments in infrastructure and manufacturing.


For instance, a $3.7 billion fertilizer plant project from Morocco signaled LDC’s, such as Ethiopia, potential to attract large-scale manufacturing projects in non-garment industries. Morocco’s Saham Finances for $375 million. Moroccan firms, the world’s largest phosphate exporter, signed at the end of 2016 a joint venture with Ethiopia to build a $3.7 billion fertilizer plant.


The government has also shown an unprecedented readiness to consolidate its democratic institutions. The government has vowed to support media practitioners and institutions operating without being defiant to professional ethics and compromising the rule of law. The media will be encouraged to seek, impart and disseminate information that would expose illicit actions and ensure accountability and good governance. The government has pledged to promote investigative journalism and guarantee the full implementation of the freedom of information Act.


Similarly, it has committed itself to dispel the preponderance of rent-seeking orientations and practices to ensure the supremacy of developmental political economy. The government also determined to dry-out the quagmire that would allow rent-seeking ideologies and tendencies to thrive. Redoubling effort in this regard would push aside the major obstacle in the journey to our renaissance.


Furthermore, the government resolved to strengthen the multi-party democracy. The ruling party has understood that excessive adversarial politics would tarnish and spoil the common mission of any political community. In fact, adversarial politics is said to create the right conditions for effective scrutiny of the government, and for genuine debate. However, when political adversaries are blindly engaged in an unbridled powers struggle driven by zero sum-game principle it would lead the democratic system to crisis. Thus, the party vowed to create platforms where it will have genuine consultation with opposition parties. Moreover, it also aimed to strengthen political participations citizens to promote deliberative democracy.


The government believes that the current rapid economic development will be sustained, accelerated and the inclusive double-digit growth is the fruit of the genuine democratic system put in place two decades ago. The need to deepen our democracy still exists and deepening our democracy is a serious matter that assumes a gravity of life and death. The government has committed itself to create a law abiding public service and officials who have the gut to uphold the public interest over and above their selfish agendas. The ruling party does not need spineless camp followers who would sell their political oath short.


Notwithstanding to the fact that we have cumbersome tasks to straighten the cultural setbacks and to unknot the meshes of backwardness, we have to take decisive steps in deepening our democracy and ensuring the sovereignty of our people through an ever increasing popular participation. We will continue to march on our developmental path and we will stop at nothing.


 


የሁለት ቀዳማዊ እመቤቶች አለም (ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ከአዜብ መስፍን) መዳብ Vs ወይዘሪት ሙስና – #ኤርሚያስ_ቶኩማ

$
0
0

እነዚህ ሁለት ቀዳማዊ እመቤቶች የብርሃን እና የጨለማ፤ የውኃ እና የእሳት ያህል ልነቶች ያላቸው ወይዘሮዎች ናቸው፡፡ የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ የነበሩት የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ባለቤት የሆኑት ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው የተወለዱት በቀድሞው የጎጃም ክፍለሀገር ሲሆን በ1968 ኮሎኔል መንግስቱን በማግባት ትዕግስት፣ ትምህርት እና አንድነት መንግስቱ የተባሉ 3 ልጆችን ያፈሩ ሲሆን በአንፃሩ ወይዘሮ አዜብ መስፍንም ከመለስ ዜናዊ ጋር ተጋብተው ሰምሃል፣ ማርዳና ሰናይ የተባሉ ሶስት ልጆችን መውለዳቸው ይታወቃል፡፡


ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው በቤተመንግስት ውስጥ በነበሩበት ወቅት በፖለቲካዊ ውሳኔዎች ላይ የነበራቸው ሚና አነስተኛ ሲሆን ብዙውን ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን እና በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እንጀራ እናት በወይዘሮ አበራሽ ዘውዴ መኖሪያ ግቢ ውስጥ የመንግሰቱን እንጀራ እናት በሽመና ስራ እያገዙ እንደነበረ ይነገራል፡፡ ወይዘሮ ውባንቺ የባለቤታቸውን ስልጣን መከታ አድርገው የህዝብ ሀብት ለመዝረፍ የሚሯሯጡ አይነት ግለሰብ እንዳልነበሩ ከሰሞኑ ተወዳጁ ጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ የኮሎኔል መንግስቱ እህትና ወንድም የሆኑትን የሺንና ደረጄን ቃለመጠይቅ ሲያደርግ መታዘብ ችለናል፡፡ የሺ ኃይለማርያም እና ደረጄ ኃይለማርያም ለጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ እንደነገሩት ከሆነ ከውባንቺ ቢሻው ቤተሰብ የመንግስቱ እህትና ወንድም በመሆናቸው ያገኙት የተለየ ጥቅም አልነበረም፤ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመንገስቱ እህት የሆነችው አመለወርቅ ኃይለማርያም አቃቂ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ውስጥ ተቀጥራ ስትሰራ የነበረች ሲሆን ወንድሞቹ ጥላሁን እና ደረጄ ሐይለማርያም ሀገራቸውን በወታደርነት እንዳገለገሉ ይታወቃል አባቱ ኃይለማርያም ወልዴ ደግሞ በስተርጅና ፋብሪካ ውስጥ ተቀጥረው በመስራት ቤተሰቡን ያስተዳድሩ ነበር፡፡ የመንግስቱና የውባንቺ ቤተሰቦች ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ጋር ተመሳሳይ ኑሮ የኖሩ ሲሆን ከቀበሌ የሚሠጠውን ዱቄትና ዘይት እንኳን እንደሌላው ዜጋ ተሰልፈው ይገዙ እንደነበረ ይገለፃል የተማሩትም ቢሆን የመንግስት ትምህርት ቤት የሆኑት ጠመንዣ ያዥ፣ ሽመልስ ኃብቴ፣ ዘርፈሽዋል፣ ምስራቅ አጠቃላይና ወንድራድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነው፡፡

በአንፃሩ የአዜብ መስፍንን ጉዳይ ስንመለከት ህወሃት ኢትዮጵያን ከወረረበት ከ1983 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የመለስ ዜናዊን ስልጣን በመጠቀም የኢትዮጵያን ህዝብ ሃብት የዘረፈች እና በጣሊያኑ ጋዜጣ ኮቲዲያኖ ጭምር ቀዳሚዋ ሙሰኛ ተብለው መሰየማቸው የሚታወቅ ሲሆን የአለም ሃብታሞችን የሀብት ደረጃ በማስቀመጥ የሚታወቀው ዘ ሪቸስት የተሰኘው ድህረገፅ ከዛሬ አራት አመት ይፋ ባደረገው መረጃ ደግሞ አዜብ መስፍን ከሁሤን አላሙዲን ቀጥሎ ኢትዮጵያ ውስጥ ሁለተኛዋ ቢሊየነር ስትሆን ፎረብስ መፅሄት ከ4 ቀናት በፊት በለቀቀው መረጃ የኢትዮጵያ 2ኛው ቢሊየነር ከበደ ከሳ የተባለ ግለሰብ እንደሆነ ቢገልፅም ከበደ ከሳ አሻንጉሊት የሆነ ግለሰብ ሲሆን በከበደ ስም የሚንቀሳቀሰው ሃብት በሙሉ የአዜብ መስፍን ሀብት እንደሆነ እሙን ነው፡፡ በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተባረሩት ምሁራን መካከል አንዱ የሆኑት ዶክተር ወንድሙ መኮንን ከጥቂት ዓመታት በፊት ለእንግሊዝ ፓርላማ የአዜብ ልጅ የሆነችው ሰምሃል መለስ ወደሶስት ቢሊየን የሚጠጋ ገንዘብ እንዳላት የሚያሳይ መረጃ ማቅረባቸውም ይታወሳል፡፡

ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ልጆቻቸውን መክረውና አስተምረው እስከ ዶክተርነት ያደረሱ እንስት ሲሆኑ ኮሎኔል መንግሥቱ ይህንኑ አስመልክተው መዳብ እያሉ ስለሚጠሯቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው የሌተናል ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ትዝታዎች በተባለው መፅሃፍ ሲናገሩ

“አሥራ ሰባት ዓመት ሙሉ በሥልጣን ላይ ስቀይ ከውባንቺና ከልጆቼ ጋር የማሳልፈው ጊዜ በጣም ውሱን በመሆኑ አንድም ቀን ሰለቸን ደከመኝ ሳትል፡ ሳትማረር የልጆቿን ትምህርትና የቤተሰቡን ጣጣ ሁሉ ብቻዋን የተወጣች ነች” ብለዋል፡፡ በአንፃሩ አዜብ መስፍን ልጆቿን እንደእናት መክራ ለወግ ለማረግ ማብቃት ሳትችል ቀርታ ልጆቿ የፈፀሟቸው አስነዋሪ ተግባራትን የሚያሳዩ ፎቶዎችን ተመልክተን መታዘባችንም ይታወሳል፡፡

ማስታወሻ:- የመጀመሪያው ፎቶ ላይ የምንመለከታቸው ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ከልጆቻቸው ጋር ነው።

 

 

The post የሁለት ቀዳማዊ እመቤቶች አለም (ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ከአዜብ መስፍን) መዳብ Vs ወይዘሪት ሙስና – #ኤርሚያስ_ቶኩማ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

“የኔታ መስፍን ምን አጠፉ?” (በመስከረም አበራ)

$
0
0
ፕ/ሮ መስፍን ወ/ልደማርያም

ፕ/ሮ መስፍን ወ/ልደማርያም

ሃገራችን ኢትዮጵያ መማር ብቻውን “ንወር ክበር!” የሚያስብልባት ምድር ነች፡፡ ተምሮ ለወገኑ ምን ሰራ? ለሃገሩ ምን አበረከተ? የሚሉት ወሳኝ ነገሮች ከክብሩ በፊት ጥያቄ ውስጥ የሚገቡ ነገሮች አይደሉም፡፡ ብዙሃኑ ምሁራን በበኩላቸው ትምህርታቸው ደሃ አደግነታቸውን የሚበቀሉበት ብርቱ በትር፣ የቅንጦት ህይወት የይለፍ የሚወስዱበት ሰልፍ ብቻ ይመስላቸዋልና ዲግሪ በደራረቡ ቁጥር ከትናንት በተሻለ ራሳቸውን ለማገልገል፣ ከሰው በልጦ ለመታየት ይታጠቃሉ፡፡ ትምህርታቸው ያልሰራውን ቁስ ከየፈረንጁ ሃገር ይሰበስባሉ፡፡ ቁሱን ይበልጥ ለማጋበስ ከግፈኛ መንግስት ጋር ማህበር ይጠጣሉ፡፡ ከደም አፍሳሽ ጋር ግንባር ይገጥማሉ፤ ከእናት ሃገር ሆድ ወጥተው የሷኑ ደካማ ጎን ይመታሉ፡፡

ከትናንት በስቲያ እግረኛ ወታደር የነበረ ኩሽሹን በከረባት ቀይሮ ባላዋቂ እጁ ሲያቦካው የኖረው ፖለቲካ እንደ ቂጣ ምጣዱ ላይ እንክትክት ሲልበት ‘ኑና ስራየ ልክ እንደ ነበረ ዱክትርናችሁን እየጠቀሳችሁ ከሙያ አንፃር አስረዱ ሲላቸው’ ሊያስረዱ ይሽቀዳደማሉ፡፡ በኢቢሲ አንድ ሁለት ቀን ካናዘዛቸው በኋላ አያያዛቸውን አይቶ፣ ፍልስፍናቸው እንደ ቅማል “እራስ ደህና” ማለት እንደሆነ አጥንቶ ለሙሉ ጊዜ አገልጋይነት ያጫቸዋል፡፡ “የዶክተሮች ካቢኔ አቋቋምኩ” ብሎ ከመጠላቱ በላይ እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ ይህም ለነሱ ክብር መስሎ ይታያቸዋልና ሹመቱ ሃሴታቸው፣ የሹመቱ ቱርፋት እርካታቸው ይሆናል፡፡

የመማር ዋና አላማው በስብ መጥገብ ከሆነ ዳርቻው ይህ ቢሆን አይስገርምም፡፡ በስብ ለመጥገብ ግን መማር ግድ አልነበረም፡፡ እንደውም ለቁስ ሰቀቀን ፍቱን መድሃኒቱ፣ የቀጥታ መንገዱ ተደራራቢ ዲግሪ የግድ የማይለው የመነገድ ማትረፉ ጎዳና ነው፡፡ መማር ግን ቁስ ከማንጋጋት፣ ሆድ ከመቀብተት ያለፈ ተልዕኮ ያለው ነገር ነው፡፡ መማር መንጋው ያላየውን ቀድሞ አይቶ ማሳየትን፣ ባልደላው ማህበረሰብ ውስጥ እውነተኛ ድሎት እንደማይኖር የመገንዘብ ራስ ወዳድነትን የመሰናበት ልዕልና፤ ለእውነት እና ለሃቅ ብቻ የመወገን እና ይሄው የሚያመጣውን ቱርፋትም ሆነ ችግር የመቀበል ልቅና ነው፡፡ ይህ ልቅና በተለይ በድሃ ሃገር እንደልብ የሚገኝ አዘቦታዊ ገጠመኝ ሳይሆን እንደ ማዕድን በመከራ ተፈልጎ የሚገኝ ብርቅ ነገር ነው፡፡

ፕ/ሮ መስፍን ወ/ልደማርያም በግብር መማራቸውን ከሚመስሉ፣ ሁሉን ከሚመረምሩ፣ ሳይደክሙ ከሚጠይቁ፤ የቁስ ምኞት የራስ ድሎት እምብዛም ከማያስጨንቃቸው ብርቆች ወገን ናቸው፡፡ ሰውየው ከጉብዝና እስከ ሽምግልናቸው ወራት ሲፅፉ ሲሞግቱ የኖሩ የሃገር አድባር ናቸው፡፡ እውቀት ልምዳቸውን በወረቀት አስፍረው፣ በቃል ተናግረው አይጠግቡም፡፡ የተናገሩ የፃፉት ለብዙ የፖለቲካችን ህማማት መልስ አለው፡፡ ሆኖም የሚታያቸውን ለማየት፣ የሚሰማቸውን ለመረዳት አቅሙም ልምዱም የሚያጥረን ሰዎች ልንወርፋቸው እንጣደፋለን፤ የምናስበውን እንዲናገሩልን እንሻለንና ብዙ ጊዜ ባልሆኑት እንከሳቸዋለን፡፡ በበኩሌ ሰው ፍፁም ነው ብየ አላምንም፤ ይህን መጠበቅም ደግ አይመስለኝም፡፡ ሰው ናቸውና ፕ/ሮ መስፍንም ሊስቱ፣ ሊያጠፉ ይችላሉ፡፡ ወይም በእኛ ግንዛቤ ያጠፉ ሊመስለን ይችላል- ሁላችንም የግንዛቤያችን ነፀብራቅ ነንና! ይሄ ጤናማ ነው፡፡

ዋናው ጉዳይ ግን ጥፋትን እና ልማትን የመመዘን እርጋታ፣ ቅሬታችንን የምንገልፅበት ሁኔታ፣በተለይ የተቃውሟችን ሁለመና ሌት ተቀን ከምናወራለትን ኢትዮጵያዊ ማንነት አንዱ የሆነውን ታላቅን የማክበር ጨዋነት ጋር አብሮ ይሄዳል ወይ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ ይሄን ያስባለኝ በተደጋጋሚ ከፕ/ሮ መስፍን ጋር በማይጥም ሁኔታ የሚሟገተው የርዕዮት ሚዲያ ባልደረባ አቶ ታምራት ነገራ ከሰሞኑ ፕ/ር መስፍን የተናገሩትን አንስቶ ከሰውየው ጋር ያለውን ልዩነት የገለፀበት ድንፋታ ነው፡፡ ራሴም በአንድ ወቅት ከፕ/ሮ መስፍን ሃሳብ ጋር ባለመስማማት ተሟግቼ ነበርና ታምራት ነገራ ለምን የፕ/ሮ መስፍንን ሃሳብ ሞገተ የሚል አቋም የለኝም፡፡ ጥያቄየ እሳቸውን ሲሞግት እንደዚህ ጣራ አድርሶ በሚያፈርጥ ንዴት የሚበግነው ለምንድን ነው የሚል ነው፡፡በእውነት እና በእውቀት፣በደንብ በገባው ነገር ላይ ለሚሞግት ሰው ጥርስ በሚያፋጭ ብግነት ውስጥ መሆን ምን ይረዳዋል? በንዴት ፈረስ ላይ ሆኖ አያት የሚሆንን ትልቅ ሰው መዘርጠጥስ አስተዳደግን ከማስገመት፤ የራስን ኪሎ ከማቅለል ያለፈ ምን ረብ አለው? ንዴት እውቀት፣ስድብ ሙግት ሆኖ አያውቅም! ማወቅ ያረጋጋል እንጅ አያንተገትግም፤ስድብ እና ዝርጠጣ ያዋቂነት ምልክት አይደለም፡፡ ስድብ የመከነ አእምሮ ውላጅ እንጅ እንደ ታምራት ነገራ ሃሳብ አለኝ ብሎ ሚዲያ ላይ ከተሰየመ ሰው የሚጠበቅ “አበጀህ” የሚያስብል ነገር አይደለም፡፡ በተለይ ፕ/ሮ መስፍንን ከመሰለ ባለ ከባድ ሚዛን ምሁር ጋር ሲሟገቱ ሰውየው የተናገሩትን በደንብ መረዳት፣መረጋጋት፣ የሚናገሩትን ማወቅ፣ራስን መግዛት ተሻይ ነው፡፡ ካልሆነ ንግግር የሚያስገምተው ራስን ነው! ስለተደጋጋመ ዝም ብየ ማለፍ ስለከበደኝ የታምራትን ጉዳይ አነሳሁ እንጅ የፅሁፌ አላማ ስላልሆነ በዚህ ትቼ ፕ/ሮ መስፍን ሰሞኑን በሲያትል ተገኝተው በተናገሩት ጠቃሚ ንግግር ዙሪያ ወዳለኝ ሃሳብ ልለፍ፡፡

ስለ ጎሳ አጥራችን ገበና፤ የልዩነት አንድነት እንዴትነት

ፕ/ሮ መስፍን ያደረጉት ንግግር የሚጀምረው በሃገራችን ወቅታዊ ፖለቲካ ዋነኛ መዘውር የሆነው አግላይ የጎሳ ፖለቲካ የሃገራችንን የማህበረ-ፖለቲካዊ ታሪክ የማይወክል ልብ ወለድ ነው በማለት ነው፡፡ይህው ስሁት እሳቤ ስህተቱን የሚያባብሰው በጎሳ መሃል አንድነት እንጅ ልዩነት የለም ብሎ ሲደመድም፤የዚህ ተቃራኒ የአንድነት አቀንቃኖች ደግሞ በሚዘምሩለት አንድነት ውስጥ ልዩነትነትን የሚያስተናግዱበት ቦታ የሌለ ወይ የጠበበ መሆኑ ነው በሚል ግራ ቀኙን የሚገስፅ እና ልብ ላለው በዚህ መሃል ያለውን አዋጭ መንገድ የሚያሳይ ነው -የፕ/ሮ መስፍን ተግሳፅ አዘል ንግግር፡፡ የጎሳ ፖለቲካ ማቆሚያ የሌለው የሽንሸና እና የማነስ ጉዞ እንደሆነም ጠቆም አድርገዋል፡፡መስማት የምንችል ብልሆች ከሆንን ይህ የፕ/ሮ መስፍን ንግግር ለፖለቲካችን ፍቱን ፈውስ የሚሆን መድሃኒት ያለው ነገር ነው፡፡

ነገሩን ከነባራዊው የሃገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታ ጋር ለማመሳከር ያህል ቆየት ካለው የኦሮሞ ጎሳ ፖለቲካ አቀንቃኞች እሳቤ አንፃር ብናየው ሰፊው የኦሮሚያ ክልል ያቀፋቸውን ኦሮምኛ ተናጋሪ ሰፊ ህዝቦችን እንደመንታ ልጆች ተመሳሳይ መልክ፣እሳቤ፣ፍላጎት ያቸው አድርጎ “ኦሮሙማ” የሚል የጅምላ ማንነት ሊያላብስ ይለፋል፤ከኦሮሞ በቀር ለኦሮሞ የሚያስብ እንደሌለ እርግጠኛ ሆኖ ‘ኦሮሞዎች ብቻ ተሰብሰቡና ምከሩ’ ሲል በር አዘግቶ ሲያስዶልት አይተናል፡፡ በዚህ እሳቤ መሰረት ኦሮሞዎች እንደነዶ ለብቻቸው ታስረው የተቀመጡ ህዝቦች ስለሆኑ እነሱ ለብቻቸው የሚወስኑት ውሳኔ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ ተፅዕኖ የለውም፤ወይም ሌላው ኢትዮጵያዊ የነሱን የብቻ ውሳኔ አሜን የማለት እዳ አለበት፡፡ኦሮሞ በተባለው ሰው ውስጥ በሚናገረው ቋንቋ ምክንያት ካገኘው አንዱ ማንነቱ (ኦሮሞነት) በቀር ሌላ ማንነት ስለሌለው ፍላጎቶቹ፣ጥያቄዎቹ፣ምኞቶቹ ሁሉ የሚመነጩት ከሚናገረው ቋንቋ ብቻ ስለሆነ መነጋገር ያለበት ከቋንቋ መሰሎቹ ጋር ብቻ ነው-እንደ እሳቤው፡፡ እውነታው ግን ሌላ ነው፡፡

የሚናገሩት ቋንቋ (ጎሳቸው) በፍፁም የማይገናኝ ሁለት በገጠር የሚኖሩ አማራ እና ኦሮሞ አርሶ አደሮችን በአንድ በኩል ሁለት ከተሜ አማራ እና ኦሮሞዎችን በሌላ በኩል አስቀምጠን ምኞት ፍላጎታቸውን ችግር ጥያቄቸውን ብንጠይቅ ከሚናገሩት ቋንቋ ይልቅ በተሰማሩበት የኑሮ ፈርጅ የተነሳ ተመሳሳይ እምነት፣ ፍላጎት፣ ጥያቄ፣ ዝንባሌ እንደሚኖራቸው አያጠራጥርም፡፡ ይሄን በጾታ፣ በእድሜ፣ በትምህርት ደረጃ ወዘተ እየተካን ብናሰላው ውጤቱ ተመሳሳይ ነው፡፡ በተጨማሪም አካባቢ እየሰፋ በሄደ ቁጥር ሰዎች ተመሳሳይ ቋንቋ እየተናገሩም ቢሆን እምነት፣ ዝንባሌ፣ ጥያቄ፣ ፍላጎታቸው በአጠቃላይ ባህላቸው ከመመሳሰል ይልቅ እየተለያየ መሄዱ ሳይንሳዊ ነው፡፡ ፕ/ሮ መስፍን ‘በጎሳ ውስጥ ልዩነት የሌለ አይምሰላችሁ’ የሚሉት እንዲህ ያለውን ጉራማይሌነት ነው፡፡ ሌላ ማሳያ ለማከል ያህል አንድ አይነት ቋንቋ መናገር አንድ ወጥ ማንነት የሚያመጣ ቢሆን ኖሮ ኦሮሞው አቶ አባዱላ የተሰለፉበት የፖለቲካ እምነት ኦሮሞውን አቶ በቀለ ገርባን እስርቤት የሚያመላልስ አይሆንም ነበር፡፡

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ከምክንያታዊነት እና ነባራዊነት ጋር ጥብቅ ጠብ የተጣላው የጎሳ ፖለቲካችን ለምክንያት የዝሆን ጆሮ ሰጥቶ ይነጉዳል፡፡ በየጎሳ ፖለቲካ “ቄሰ-ገበዙ” አቶ ጃዋር መሃመድ በአንድ ወቅት አቶ አባዱላ ገመዳ ዛሬ ኦ.ኤም.ኤን ካባረረው ጋዜጠኛ አብዲ ፊጤ እና ሌሎች ጋር የነበራቸውን እራት ግብዣ አስመልክቶ ‘እንዴት የኦሮሞ ወጣቶችን ከሚያስረው ሰው ጋር ማዕድ ትቀርባላችሁ?’ በሚል ትችት ሲቀርብበት ‘ኦሮሞ ሁሉ ወገናችን ነው አበሾች በልዩነታችን ማትረፍ ስለምትወዱ እኛ ስንሰባሰብ አትወዱም’ ሲል መልስ በሰጠ አንድ አመት ሳይሞላው ነው ኦህዴድ በሚመራው የኦሮሚያ ክልል የዚያ ሁሉ የኦሮሞ ደም የፈሰሰው፡፡ ጃዋር ባለው መሰረት ኦሮሞ ሁሉ የኦሮሞ ወገን፤ ኦሮሞ ያልሆነ ሁሉ ለኦሮሞ የማይተኛ ከሆነ ለምን ኦህዴድ በሚመራው ክልል፤ወገኔ ብሎ እራት ያቋደሳቸው አቶ አባዱላ ዋና በሆኑበት ስርዓት ያሁሉ ኦሮሞ ሞተ፣ ጃዋርስ እንዴት የሞት ነጋሪት ጎሳሚ ተደርጎ በስሙ ፋይል ተከፈተ? ‘ይህን መዛባት አጢኑና ወደ መስመር ግቡ’ ነው የፕ/ሮ መስፍን ምክርና ተግሳፅ፡፡

የአማራ ብሄርተኝነት ለማስፈን የሚለፉ የአማራ የጎሳ ፖለቲከኞች እንደ ኦሮሞ ጓዶቻቸው አንድ አማራዊ ማንነት አለን እንጅ ጎጃሜ፣ጎንደሬ፣ወሎየ፣መንዜ አትበሉ ይላሉ፡፡እኔን ጨምሮ አብዛኛው ኢትጵያዊ ደግሞ ይበልጥ የሚያውቀው ጎጃሜ፣ጎንደሬ፣ተጉለቴ የሚለውን እንጅ አማራ የሚለውን ማንነት አይደለምና ይህም ትልቅ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሆኖ ያነታርካል፡፡እንዲህ ብሎ ለያይቶ መጥራት የአማራን ህዝብ ማንነት የማጥፋት ሂትለራዊ ተንኮል ተደርጎ ይወገዛል፡፡ የአማራ ህዝብ ራሱ ግን ይህ ውድቅ የሚያደርግ በልጅነቴ እየሰማሁት ያደግኩት አንድ አባባል አለው -“የጎንደሬን አማርኛ እንኳን መንዜ ጎጃሜም አይሰማው” ይላል፡፡አባባሉ የሚያስረዳው በአሁኑ የሃገራችን የጎሳ ፖለቲካ ፈሊጥ የፍፁም መመሳሰል ዳርቻ እየተደረገ ባለው በአንድ አይነት ቋንቋ በመግባባት ውስጥ እንኳን ልዩነት መኖሩን ነው፡፡ እንደሚባለው አማራነት፣ከአማራ ምድር መወለድ እንደ ፋብሪካ ምርት አንድ የሚያደርግ፣ ሁሉን ፍጡር አንድ አይነት ነገር የሚያሳስብ ከሆነ በትቂቱ ቤተ-አማራ ከሞረሽ ወገኔ ተለይቶ አናየውም ነበር፡፡ እውነታው እና የሚያስኬደው መንገድ ፕ/ሮ እንዳሉት ሰው ባለበት ሁሉ ልዩነትም አንድነትም መኖሩን ተቀብሎ የማያልቀውን የጎሳ አጥር እያጠበቡ ሲያጥሩ ከመኖር እልፍ ማለቱ ነው፡፡

የጎሳ ፖለቲካ አጥር ማለቂያ የለውም የሚለው አባባል አሁንም ሰከን ብሎ ለሰማ፣ሰምቶም ለመማር ለተዘጋጀ ጥሩ ጥቁምታ ነው፡፡ ይህን ነገር ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በአንድ ወቅት “በዘር ፖለቲካ ሄደህ ሄደህ የምትገባው ቤትህ ነው” ካለው ግሩም እይታ ጋር መሳ ነው፡፡ ነገሩን ወደ ነባራዊው የሃገራችን የጎሳ ፖለቲካ ሃቅ ስንመልሰው እኔ የምኖርበት የደቡብ ክልል በርካታ ብሄረሰቦችን ያቀፈ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ለስራ ጉዳይ ከክልሉ ብሄር የአንዱ ተወላጅ ከሆነ ሰው ጋር እሱ ተወልዶ ባደገበት የገጠር ቀበሌ የኔ መስሪያቤት የሚሰራው ስራ ኖሮ ከእኛ ጋር ይጓዝ ነበር፡፡እናም የሄድንበትን ስራ ጨርሰን የእርሱን የትውልድ መንደር ለቀን ግን በዛው ዞን ውስጥ ከትውልድ መንደሩ አንድ አስር ኪሎሜትር ርቀን እንደተጓዝን አንዲት ትንሽ ከተማ እንደደረስን ሰውየው “እኔኮ እዚች ከተማ ልጄን ማስቀጠር አልችልም” ብሎ ዝምታችንን የሚሰብር ንግግር አመጣ፡፡ “ለምን አንድ ዞን አይደል እንዴ?” አልኩኝ በጣም ስለገረመኝ ተሸቀዳድሜ፡፡ “አንድ ዞን ቢሆን፣ ቋንቋው አንድ ቢሆን ጎሳችን ግን የተለያየ ነው፤ እነሱ ጎሳቸው ያልሆነን ሰው አበጥረው ያውቃሉና የኔ ልጅ ይወዳደር ይሆናል እንጅ መቀጠር የማይታሰብ ነው” ሲል የደረስንበትን አዘቅት ቁልጭ አድርጎ አሳየኝ፡፡ ቀጥየ ጥያቄ አላነሳሁም፤ዝም ዝም ሆነ! የሚያፅናናው ነገር ግን ፕ/ሮ እንዳሉት የጎሳ ፖለቲካ ቀሳውስት ለስልጣን እና ለጥቅም ዘር እያቋጠሩ ሃረግ ሊያማዝዙት ቢሞክሩም የኢትዮጵያ ሰፊ ህዝብ ግን እየተጋባ እየተዋለደ ኢትዮጵያዊነቱን በሰውነቱላይ፤ዜግነቱን በኢትዮጵያዊነቱ ላይ እያፀና “ሃዘንህ ሃዘኔ፤ደምህ ደሜ” እየተባባለ በሩቅ እየተነጋገረ ይኖራል፡፡ ይህ ሁሉ ዘመን አመጣሽ እትብት የመማዘዝ ፖለቲካ የመጣውም በትቂቶች ነውና ፅናት አይኖረውም፤እነዚህ ትቂቶች የመሰረቱት ክፉ አግላይ ስርዓት በስብሶ ሲወድቅ ሁሉም ይስተካከላል፡፡

ቂም፣ ልግም፣ የክፋት አዙሪት – ቆሞ መቅረት!

ፕ/ሮ መስፍን እንደህዝብ ያለብንን ችግር በደንብ ተረድተው፣ የተረዱትን እውነት በሚገባን፣ መሬት በወረደ ቋንቋ ተርጉመው ጉድፋችንን በማስረጃ አበልፅገው በማንክደው ሁኔታ በማሳየት ተወዳዳሪ የሌላቸው ምሁር ይመስሉኛል፡፡ “የኔታ” የሚለው የኢ-መደባዊ ማዕረጋቸው ትርጉምም ይሄው ይመስለኛል፡፡ የኔታ የሚለው ማዕረግ ፊደል ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን የመገሰፅ የመኮርኮም ሞራላዊ ስልጣንንም ይይዛል፡፡ ፕ/ሮ መስፍን በማህበረ-ፖለቲካዊ ችግሮቻችን እና በመፍትሄዎቻቸው ዙሪያ በአማርኛም በእንግሊዝኛም በደንብ ፅፈዋል፡፡ፅፌያለሁ ብለው መናገራቸውንም አይተውም፡፡ የፃፉ የተናገሩትን ወጣቱ ትውልድ እንዲያነብ፤በትኩረት እንዲያደምጥ ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኛው የዘመናችን ጋዜጠኛ፣ፖለቲከኛና ተንታኝ ደግሞ ማንበብ ላይ ወገቤን ባይ ስለሆነ የተናገሩ የፃፉት የሚመልሰውን ጥያቄ ይዞ ወደ እሳቸው ሲመጣ ይቆጣሉ፤ይገስፃሉ፡፡ “ቁጣው የፃፍኩትን ሁሉ አሜን ብላችኑ እመኑ” ከማለት አይመስለኝም፡፡ አንብቦ “እርስዎ በመፅሃፍዎ እንዲህ ብለዋል ግን እኔ እንዲህ ይመስለኛል” ለሚላቸው ቦታ የሌላቸው ሰው አይደሉም፡፡ ሳያነቡ፣በውል ሳያዳምጡ ከበሬ ፊት ሊበሉ ለሚመጡ ጥጆች ግን ትዕግስት የላቸውም፡፡ ቁጣቸው ይነዳል፡፡ በበኩሌ ቁጣው አያስቀይመኝም፤ይልቅስ ከመናገር ከመፃፋችሁ በፊት አንብቡ የማለት የታላቅ ምክር አድርጌ እወስደዋለሁ፡፡

ፕ/ሮ ረዥም የህወት ልምዳቸው እና ምጡቅ ታዛቢነታቸው እንዳቀበላቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ግፈኛን የሚያሸንፍባቸውን ዘዴዎች አሳይተውናል፡፡የኢትዮጵያ ህዝብ ግፍ ሲበዛበት ያቄማል፣አቂሞ ይለግማል፣ ለግሞም አይቀርም ጊዜ ጠብቆ ቂሙን ክፉን በክፉ በመመለስ ተንፈስ ያደርጋል፡፡ ክፉን በክፉ ሲመልስ የሚጠላውን፣የተቃወመውን ክፋት ራሱ መልሶ ያደርገዋል፡፡ ይህ አካሄድ ውጊያው ከክፋተኛው ግለሰብ እንጅ ከክፉ አስተሳሰቡ ስላልሆነ ክፋተኛ ነቅሎ ሌላ ክፋተኛ ይነተክላል፡፡ ስለዚህ የሃገራችን ፖለቲካ ከክፋት አዙሪት ሊወጣ አልቻለም ይላሉ፡፡ መፍትሄውን ሲያስቀምጡ መዋጋት ያለብን ክፋትን ራሱን አስተሳሰቡን መሆን አለበት፡፡ ይህ መንገድ በደንብ ገብቶን ከጀመርነው ክፋትን ለማጥፋት ሌላ ክፋትን እንደመሳሪያ አድርገን መጠቀም እናቆማለን ይላሉ፡፡ ክፉ አስተሳሰብን ለመዋጋት ደግሞ ከራስ ጋር ብቻ የማውራት አድፋጭነትን አስወግደን መነጋገርና መግባባት መጀመር አለብን፡፡ እስከዛሬ ሳንነጋገር ስንግባባ የኖርነው ክፋትን በክፋት በመመለሱ ማድፈጥ ውስጥ ባለ ክፉ ቋንቋ ነው፡፡ አሁን ግን እርስበርስ ተነጋግረን ከሃሳባችን ፍጭት ክፉን በክፉ ከመቃወም የተለየ፣የተሻለ፣የዘመነ መንገድ ማውጣት አለብን ባይ ናቸው-የኔታ መስፍን!

 

ሌላ ሳንካ…..!

ጨቋኝ መንግስታትን ለመንቀል ስንታገል የግፍ አስተዳደርን እሳቤ፣ክፋትን ራሱን በፅንሰሃሳብ ደረጃ ተቃውመን፤ክፉን ካስወገድን በኋላ በጎ የመትከሉ ነገር ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን እስከ ዛሬ አልተቻለንም፡፡ ለምን ቢባል ክፉን ለመንቀል የሚያስችለን የቂም፣የልግመኝነት እና ክፉን በክፉ የመመለስ ሃይል በሙላት ስላለን ክፉን መንቀል ችለናል፡፡ እነዚህ ክፉን ለማስወገድ ሃይል የሆኑን ነገርግን ቂም፣ልግመኝነት፣ማድፈጥና፣ክፉን በክፉ መመለስ በጎ ስርዓትን ለመትከል የሚያስችል ልዕልና የሌላቸው፤ለዘመነ ፖለቲካ ስፍነት፣የተሻለ አኗኗር እውንነት የማይመጥኑ ኋላ ቀር እና ተራ ልምዶች ስለሆኑ ፖለቲካችንን ቆሞ-ቀር አድርገውታል፡፡ እስከዚህ ድረስ ከፕ/ሮ መስፍን ጋር እስማማለሁ፡፡ ነገር ግን ለፖለቲካችን ቆሞ መቅረት ሃላፊነቱን መውሰድ ያለበት አካል በየፈርጁ መታየት ያለበት ይመስለኛል፡፡

እንደሚታወቀው አብዛኞቹ በኢትዮጵያ የተካሄዱ ጨቋኝ አስተዳደርን የማስወገድ እንቅስቃሴዎች ወጣኔያቸውን እና ፍፃሜያቸውን የሚያገኙት ከፖለቲካ ልሂቃን ሆኖ ህዝቡ የሚፈለገው መሃል ላይ ለለውጡ ጉልበት ለመስጠት ሲባል ነው፡፡ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን የመጣበትን ሁኔታ ብናይ ፕ/ሮ መስፍን እንዳሉት በማራቶን ሩጫ ሃገሪቱን ከመቆጣጠሩ በፈት የህዝቡን እርዳታ ማግኘት ምትክ የሌለው ወሳኝ ጉዳይ ነበር፡፡ወደ አፈሙዝ ላንቃ የሚማገድ እግረኛ ወታደር ወልዶ መስጠቱ፣ ለወታደሩ እህል ውሃ ማቅረቡ፣ቁስለኛ ማስታመሙ፣ የጠላትን ሁኔታ ሰልሎ መረጃ ማቀበሉ፣ ጠላት ገፍቶ ሲመጣ መደበቅ መሸሸጉ ሁሉ ኢህአዴግ በመጨረሻዎቹ አመታት ወደ አዲስ አበባ ለመገስገስ ያስቻሉት ቀደም ብሎ ያገኛቸው የህዝብ ድጋፎች ነበሩ፡፡ ‘ህዝቡ ይህን ድጋፍ ለምን ሊያደርግ ቻለ?’ ለሚለው ጥያቄ አንዱ መልስ ፕሮፌሰር መስፍን ያነሱት በግፈኛ ላይ የማቄም፣የመለገም፣ክፉን የመበቀል ዝንሌ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ሆኖም ህዝቡ ይህን ሲያደርግ ‘በወታደር ጫማ እየረገተህ ያለውን ክፉ ጥለን ዲሞክራሲን እናመጣልሃለን’ ያሉትን ሸማቂዎች አምኖ የተሻለ ያደርጉልኛል ብሎ ተማምኖ ይመስለኛልና ክፉን ነቅሎ ደግ ባለመትከል እጅግም መወቀስ ያለበት አይመስለኝም፡፡ ክፉ ነቅሎ በጎ ባለመትከል መወቀስ ያለበት ዲሞክራሲ ላመጣልህ እታገልኩ ነው ብሎ የህዝብን አጥንት እየጋጠ፣በህዝብ ጫንቃ ላይ እየተረማመደ ለስልጣን የበቃው የትናንት ነፃ አውጭ ነኝ ባይ ሸማቂ የዛሬ ተረኛ ግፈኛ አስተዳደር ይመስለኛል፡፡

ይህ አካል በቃል አባይነት፣በመሰሪነት እና በአታላይነት መወቀስ፤ለፖለቲካችን ቆሞመቅረት የአንበሳውን ድርሻ መውሰድ አለበት፡፡ህዝባችን በየዋህ ልቦናው አምኗቸው የመሶብ የቡኾእቃውን ገልብጦ እንዲያበላቸው፣ ልጆቹን ለሞት መርቆ እንዲሰጥ ያደረገው የሸማቂዎቹ አስመሳይነት ነበር፡፡ ሸማቂዎቹ የልባቸውን እሲኪያደርሱ፤እንጦጦ አፋፍ እስኪደርሱ ዲሞክራትነታቸውን ለየዋሁ ህዝብ የሚያስረዱት “ቅጫማም” እየተባሉ ሲሰደቡ ዝም በማለት፣ “የተሰማችሁን ተናገሩ መብታችሁ ነው” በሚል ሽንገላ፣ሌባ የተባለን ሁሉ ያለፍርድ በየመንገዱ በጥይት በመቁላት ወዘተ እንደ ነበር ያየ የሰማ የሚናገረው ነው፡፡ያለፍርድ ሌባ የተባለን ሁሉ አስፋልት ላይ ሲያጋድሙ የነበሩት የፍትህ አለቃ ነን ባዮች በወንበራቸው ሲደላደሉ መንግስታቸው የሌባ መርመስመሻ እንደሆነ ራሳቸው ‘የመንግስት ሌባ ከቦናል’ ሲሉ በፓርላማ መስክረዋል፡፡ተራ ስድብ ሲሰደቡ ዝም ሲሉ እንደ ባህታዊ ይቃጣቸው የነበሩ ሸማቂዎች ዛሬ ጋዜጠኞች ስራቸውን ስለሰሩ ብቻ የሚያስሩ ፈርኦኖች ወጥቷቸዋል፡፡ ‘ደርግ የሰማኒያ አመት ሽማግሌ አሰረ ብለን ደደቢት ነጎድን’ ያሉ የነፃነት ነብያት ነን ባዮች ዛሬ የሰማኒያ አመት ሽማግሌ አስረው ቦክስ የሚያቀምሱ “ጎበዞች” ፤እናትን በልጇ አስከሬን ላይ አስቀምጠው የሚደበድቡ ጉዶች ሆነዋል፡፡

ከላይ በተንደረደርንበት ነባራዊ ሃቅ ላይ ቆመን ለፖለቲካችን ቆሞ-መቅረት፣አልለቅ ላለን የክፉ አስተዳደር አዙሪት ስፋኔ ዋነኞቹ ተጠያቂዎች የትናንቶቹ የነፃነት ታጋይ፣የእኩልነት አደላዳይ፣የዲሞክራሲ ነብይ ነን ባዮቹ ሃገራችን የፖለቲካ ልሂቃን መሆን አለባቸው ብየአስባለሁ፡፡ የእነዚህ አካላት አታላይነት፣አስመሳይነት፣ግብዝነት እና መሰሪነት ፕ/ሮ መስፍን ለፖለቲካችን ክፉ አዙሪት በምክንያትነት ካነሷቸው ቂመኝነት፣ልግም፣ማድፈጥ፣እና ክፋት እኩል ፖለቲካችንን የክፋት አዙሪት ውስጥ የከተቱ መሆናቸው ታውቆ ለፈውሳችን መላ መባል አለበት፡፡

ያልተስማማኝ….

ከላይ እንደተቀስኩት ፕ/ሮ መስፍን እግራቸው ስር ቁጭ ብለን የፃፉ የተናገሩትን ልናስተውል የሚገባን ድንቅ መካር ናቸው፡፡ ብዙ የሚያመርት ፈጣን ጭንቅላት ያላቸው፣ፍርሃት የማያውቃቸው፣ብዙ ምሁራንን የሚያንገላታው የቁስሰቀቀን ሲያልፍም የማይነካካቸው፣ ሃገር ወዳድ አድባር እንደሆኑ አያነጋግርም፡፡ሆኖም ከሃሳባቸው ጋር አለመስማማትም ሆነ በከፊል መስማማት ተፈጥሯዊም ጤናማም ነው፡፡ግን አለመስማማታችንን ስንገልፅ ሽምግልናቸውን ብቻ ሳይሆን አዋቂነታቸውን የሚመጥን ክብር ልንነፍጋቸው አይገባም፡፡ ለትልቅነታቸው ያለኝ ክብር እንዳለ ሆኖ፤በንግግራቸው ብዙ በመማሬ እያመሰገንኩ ከንግግራቸው ያልተስማሙንን አንድ ሁለት ነጥቦች ላንሳ፡፡ አንደኛው ከላይ የጠቀስኩት ህዝቡን እና አታላዩን ልሂቅ በአንድ ላይ አይተው ለፖለቲካችን ክፉ አዙሪት በእኩል ተጠያቂ ያደረጉበት መንገድ ቢነጣጠል እና ልሂቁ እንደጥፋቱ መጠን ትልቁን ሃላፊነት ቢወስድ የሚል ነገር አለኝ፡፡ ፕ/ሮ መስፍን የሚሉት በጎ ስርዓትን ለመትከል ሚገፋውን በጎ ሃይል ያጣው አስመሳይ መልቲነትን ተከናንቦ ስልጣን ላይ ቂጢጥ ያለው ልሂቅ ነው፡፡ ‘ህዝቡስ በዚህ አዙሪት ውስጥ ድርሻ የለውም ወይ?’ የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም ህዝቡ ከተወቀሰ የሚወቀሰው በደርሶ አማኝነቱ ምክንያት ለልሂቁን ብልጣብልጥነት መረዳት ባለመቻሉ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ የግንዛቤ ነገርም ስላለበት በብዛት ላልተማረው ህዝባችን ይቅርታ ለማድረግ በቂ ምክንያት ነው ብየ አስባለሁ፡፡ ህዝቡ ሸማቂዎች ስልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ቃልአባይነታቸውን ተረድቶ ለምን በጊዜ አይሸኛቸውም የሚል ሌላ ጥያቄ ከመጣ ህዝቡ ይህን የሚያደርግበት የህግ የበላይነት፣ለይስሙላ ህግ በወረቀት ከመቸከቸክ ባለፈ ህግን የሚያስፈፅም ተቋማዊነት እንዳይኖር የልሂቃኑ አታላይ የፖለቲካ ማንነት ስላልፈቀደ፤ህዝቡ ገፍቶ ሲመጣም ልሂቁ በጥይት ቋንቋ ስለሚያናግረው አሁንም ወደ ማድጥፈጡ ከመመለስ ያለፈ አማራጭ የለውም፡፡ ስለዚህ ትልቁ ስራ የቀረው ስልጣን ላይ ካለው የፖለቲካ ልሂቅ ይመስለኛል፡፡

ሁለተኛው ጥቅሙን ያጣሁት የፕ/ሮ መስፍን ንግግር ስለ በላይ ዘለቀ እና አፄ ኃ/ስላሴ፤ ኦሮሞነት ስለ ኃ/ማርያም የወላይታ የመጀመሪያው ባለስልጣን ያለመሆን ጉዳይ ያነሱት ነገር ነው፡፡ ይሄ በተለይ እንደ እርሳቸው ለሰብአዊ ፍጡር ሁሉ መብት ለሚሟገት፤ይህንንም በሃገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቋም መስርቶ በማስኬድ ለሚወደስ የሰብዐዊነት ምልክት ሰው አይመጥንም፡፡ ለፖለቲካችን ፈውስም አስፈላጊነቱ አይታየኝም፡፡

 

የምንጣፉ ውበት!!!!

ፕ/ሮ መስፍን በንግግራቸው መጨረሻ ላይ በሃገራችን የፖለቲካ ወለል ላይ መነጠፍ ስላለበት በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በህግ ስርዓት የተማገረ ውብ ምንጣፍ የተናገሩት ውብ ንግግር በጣም ድንቅ ነው፡ ፡ምንጣፉ ዜጋን ሁሉ በእኩልነት የሚያንከባልል መሆን እንዳለበት፤ ሆኖም የሚንከባለሉ ሰዎች ወደ ምንጣፉ ሲመጡ ምንጣፉን እንዳያቆሽሹና ወደ ተለመደው አዙሪታችን እንዳይጨምሩን አእምሯቸውን፣ ከቂም በቀል ማፅዳት፣ ከክፋት መፈወስ አለባቸው ይላሉ፡፡ ነገሩ ድንቅ ነው፡፡ ሆኖም ጉዳዩን ከምኞት ባለፈ ገቢራዊ ለማድረግ ደግሞ የፖለቲካ ንቃትን በህዝቡ አእምሮ ውስጥ ማስረፅ አስፈላጊ እንደሆነ በደንብ ሊጤን ይገባል፡፡ አእምሮን የሚያቆሽሽ፣ ክፋት የሚሞላ፣ጨለምተኝነት፣ ጠጠራጣሪነት፣ ቂም በቀልን የሚያሸክም፣ በምኞት ፈረስ የሚያስጋልብ፣ በልቼ ልሙት የሚያስብል ራስ ወደድነት፣ የህግ ማህበረሰብ ያለመሆን፣አምባገነንን ለመሸከም የማጎንበስ አድርባይነት ሁሉ ምንጩ አለማወቅ ነው፡፡ ስለዚህ በሃገራችን የሲቪክ ማህበራት እንደልብ ተንቀሳቅሰው ህዝቡን ስለመብቱ፣ ግዴታው፣ ከመንግስት ጋር ሊኖረው ስለሚገባ ተገቢ ግንኙነት እንዲያስተምሩ መሆን አለበት፡፡ ይሄኔ የነቃው ህዝብ ዲሞክራሲ መብቱን ለማስከበር ተቋማትን ገንብቶ ለመብቱ ተቋማዊ ጠበቃ ያቆማልና አምባገነን እየተፈራረቀ ሊያስጨንቀው አይችልም፡፡

The post “የኔታ መስፍን ምን አጠፉ?” (በመስከረም አበራ) appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


እስቲ ጠይቁልኝ! – አቻምየለህ ታምሩ

$
0
0

ወያኔ ደብረ ብርሀን ላይ በከፈተው የአእምሮ ማጫጫ የፖለቲካ ማዕከል [ዩኒቨርሲቲ ላለማለት ነው] «ዳግማዊ ምኒልክ ካምፓስ» በሚል ስም የመሰረት ድንጋይ ለወደቀለት ትውልድ ማምከኛ ካምፕ የትግራይ ካድሬዎች እነ ዳንኤል ብርሀነ «ንጉሱ የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመዋልና በሳቸው ስም በየተሰየመ ካምፓስ ውስጥ አዲስ ገቢ ተማሪ መማር አልፈልግም ቢል እንዴት ይታያል?» ሲሉ ዘመቻ ከፍተዋል።

አቻምየለህ ታምሩ

የወያኔ ካድሬዎች ሰው ሁሉ እንደነሱ ደንቆሮና ማገናዘብ የተሳነው ይመስላቸዋል። ይሄ እነሱ «ንጉሱ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ፈጽመዋል» የሚሉት ነገር ሁሉኮ የተፈጸመው ወያኔ ሀውልትና ትምህት ቤት ያቆመላቸው ዓፄ ዮሐንስ አራተኛ ንጉሰ ነገሥት በነበሩበት [ያኔ ምኒልክ ንጉስ ነበሩ] ዘመንኮ ነው። ፖለቲካቸው ጸረ እውቀት፣ የዘርና የዐማራ ጥላቻ ስለሆነ ዓፄ ዮሐንስ አራተኛ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ሆነው በኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጸመ ለሚሉን «የሰብዓዊ መብት ረገጣ» የአንዱን ጠቅላይ ግዛት[ የሸዋን] ገዢ ንጉስ ምኒልክን ተጠያቂ ያደርጋሉ። ይገርማልኮ! ወያኔ ሐውልት ያቆመላቸው የጨለንቆም ሆነ የአኖሌ እየተባሉ የሚነገሩት ጦርነቶችኮ የተካሄዱት በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ሳይሆን ዓፄ ዮሐንስ አራተኛ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት በነበሩበት ዘመንኮ ነው። እና በምን መስፈርት ነው በዓፄ ዮሐንስ አራተኛ ንጉሰ ነገሥት ዘመን በሆነው ንጉስ ምኒልክ ተወቃሽ ተደርገው «ንጉሱ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ፈጽመዋል» ሊባሉ የሚችሉት?

ምን ይሄ ብቻ! እነዚህ ካድሬዎች ምኒልክን «በየሰብዓዊ መብት ረገጣ» እየከሰሱ እነሱ ተጨማሪ ሀውልት እንዲቆምላቸው፤ ግዛት እንዲሰየምላቸው ዘመቻና ቅስቀሳ የሚያካሄዱላቸውና «የኛ ናቸው» የሚሏቸው እነ ዓፄ ዮሐንስኮ «ጎጃም ተቃጠለ ከአባይ እስከ አባይ፣ ትግሬ ቅጠል ይዞ ሊያጠፋው ነው ወይ?» የተባለላቸው፤ በነ ዳንኤል ብርሀነ አገላለጽ «ከሰብዓዊ መብት ረገጣ» አልፎ ጎጃምን በሙሉ ያጠፉ፤ ወሎን የጨፈጨፉና የዋጉን ተክለ ጊዮርጊስን አይን በእጃቸው አፍርጠው በዱልዱም በማረድ ዘግናኝ ጭካኔ የፈጸሙ ናቸው።

ምን ይሄ ብቻ! የተከዘ ማዶ ካድሬዎች በየቦታው ሀውልት እንዲቆምላቸውና ትምህርት ቤት እንዲሰየምላቸው የሚቀሰቅሱላቸውና «የኛ ናቸው» የሚሏቸው እነ ራስ አሉላ አባነጋኮ «ሰብዓዊ መብት ረገጣ» ብቻ ሳይሆን ጦርነት በሌለበት ሁናቴ ሰላማዊ ሕዝብ በመውረር ፌቫሊና ሮይ ፓተማን «Blood, Land, and Sex፡ Legal and Political Pluralism in Eritrea» በሚል ርዕስ ባሳተሙት መጽሀፍ ገጽ 36 ላይ እንደገለጽው እ.ኤ.አ. በ1886 ዓ.ም. በባህረ ነጋሽ ባርካን ክልል ባካሄዱት ወረራ ሁለት ሶስተኛውን የኩናማና የናራ ህዝብ እንደጨፈጨፉ አስከፊውን ጭፍጨፋ ተከትሎ የተካሄደውን ጥናት ጠቅሰው አቅርበዋል።

እና እንግዲህ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመዋልና በሳቸው ስም በየተሰየመ ካምፓስ ውስጥ አዲስ ገቢ ተማሪ መማር አልፈልግም ቢል እንዴት ይታያል?» ከተባለ መታየት ያለበት የምኒልክ ብቻ ሳይሆን በዓፄ ዮሐንስ አራተኛና ራስ አሉላ አባ ነጋ ስም የተሰየመውና የሚሰየመው ሁሉ ነው መሆን ያለበት። በዚህ በማይዋሽበት ዘመን ሲያቃጥል በማንኪያ፤ ሲቀዘቅዝ በእጄ አይሰራም! ኢትዮጵያስ ዳግማዊ ምኒልክ በግፍ የመሰረቷት አገር ከሆነች ለምን ሁላችን ወደነበርንበት ከግራኝ በፊት ወደነበረው ይዞታችን አንመለስም?

በምኒልክ ከተማ በአዲስ አበባና በመላው በአገሪቱ ተንፈላሰው ደልቷቸው ተዘባነው እየኖሩ «ንጉሱ የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመዋልና በሳቸው ስም በየተሰየመ ካምፓስ ውስጥ አዲስ ገቢ ተማሪ መማር አልፈልግም ቢል እንዴት ይታያል?» የሚሉትን የትግራይ ካድሬዎች እስቲ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ጠይቁልኝ፤

1. «ዳግማዊ ምኒልክ » በሚል በተሰየመ ካምፓስ ውስጥ «ንጉሱ ሰብአዊ መብት ረገጣ ስለፈጸሙ» ተማሪ መማር ላይፈልግ ይችላል ካላችሁ የናንተው ድርጅት ወያኔ ምኒልክ ቤተ መንግሥት ውስጥ ምን ይሰራል? ሁሉ ነገር ከራስ ይጀምራል እንደሚባለው «ሰብአዊ መብት በፈጸሙት» በምኒልክ ቤተ መንግሥት ውስጥ ፋሽስት ወያኔ ለምን ይኖራል? እስቲ መጀመሪያ እናንተ «ሰብአዊ መብት ረገጡ» ካላችኋቸው ከምኒልክ ቤተ መንግሥት ውጡና ለመርሃችሁ መገዛታችሁን አሳዩን?

2. እናንተ የትግራይ ካድሬዎች «ምኒልክ የሰብአዊ መብት ረገጣ ስለፈጸሙ በሳቸው ስም በየተሰየመ ካምፓስ ውስጥ አዲስ ገቢ ተማሪ መማር የለበትም» ስትሉ ያነሳችሁት «ተጠይቅ» የመርህ ጉዳይ ከሆነ፤ ምኒልክ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው» በገነቡት አገር ውስጥ፤ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው» በቆረቆሩት ከተማ ውስጥ እናንተ ምን ትሰራላችሁ? ለምንስ እናንተ የትግራይ ሰዎች ተከዘን ተሻግራችሁ፤ ወሎና ሸዋን አልፋችሁ ምኒልክ የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው በገነቡት አገር፤ በቆረቆሩት ከተማ በአዲስ አበባ ውስጥ ትኖራላችሁ?

3. «ዳግማዊ ምኒልክ ካምፓስ» በሚል ስም የመሰረት ድንጋይ በወደቀለት ትውልድ ማምከኛ ካምፕ ውስጥ ንጉሱ ሰብአዊ መብት ስለፈጸሙ ተማሪ መማር ላይፈልግ ይችላል ካላችሁ ለምን ይህ ጉዳይ ከናንተ አይጀምርና ምኒልክ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው» በገነቡት አገር፤ በቆረቆሩት ከተማ መኖር አንፈልግም ብላችሁ ወደ ትግራይ አትገቡም? እናንተ የሰብአዊ መብት መምህሮች ሰብአዊ መብት ተረግጦ በተገነባ አገር ውስጥ ለምን ትኖራላችሁ?

4. የናንተ ድርጅት ፋሽስት ወያኔስ ለምን ምኒልክ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው» አንድ ያደረጉትን አገር ይገዛል? እንዴትስ ብሎ ምኒልክ «የሰብአዊ መብት ረገጣ ፈጽመው» አንድ ካደረጓቸው «ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች» ግብር ይሰበስባል? እስቲ ጠይቁልኝ!

The post እስቲ ጠይቁልኝ! – አቻምየለህ ታምሩ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

የአዜብ ጎላ ዋነኛ ገንዘብ ደባቂዋ ተጋለጠች! – አስናቀው አበበ

$
0
0

የአዜብ የእክስት ልጅ የአዜብ ጎላ ብር አስቀማጭና አንቀሳቃሾች ውስጥ አንዷ መሆኗን Forbes አስነቃባት። ሃፍታም “ኢትዮጵያዊያን” ተብለው አንድ አምስት ሰወች ስማቸው ቢደረደርም “አኪኮ ስዩም አምባዬ” የተባለችው ቁጥር አንድ ላይ ተሰድራለች። ከአሁን በፊትም አዜብ ጎላ የናጠጡ ሃብታም ተርታ በይፋ መዘገቧ ይታወቃል። እነዚህ የእፉኝት ልጆች ምን ያክል እንደቦጠቦጡን ተመልከቱ። እነዚህን የገቡበት ገብተን ጨርሰው ሳያጠፉን ካላስወገድናቸው አጥንታችንም አይተርፍ።

እናም የመለስ ዜናዊ ሚስት የአዜብ ጎላ የአክስት ልጅ የሆነችው አኪኮ ስዩም የኦርካይድ ቢዝነስ ግሩፕ ( Orchid Business Group , OBG ) መስራችና ባለቤት እንደሆነች ተጠቅሷል። ሸፍጡ አዜብ ጎላን ለመከለል እንደሆነ የማይታበል ነው። ይህ ኩባንያ በመንገድ ስራ ተቋራጭነት ፣ በኮንሰትራክሸን ዕቃዎች አቅራቢነት እና ኪራይ ላይ የተሰማራ ነው ተብሏል።
ይህች ስሟንም ሰውነቷንም ድልት እንዲለው ያደረገች ምስጥ ፎቶዋን እዩትና ለሃገራችን መራቆት አንዷ ባለወፍራም ባለእዳ መሆኗን አስምሩበት።

The post የአዜብ ጎላ ዋነኛ ገንዘብ ደባቂዋ ተጋለጠች! – አስናቀው አበበ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.

Beauty and Color: Amazing HD Photos of Ethiopia’s Attractions

$
0
0

Ethiopia is home to more than 100 million people—the second most-populous nation in Africa. It is also composed of wildly varying landscapes, and an incredible diversity of ethnic and religious groups. Getty Images photographer Carl Court reports that “Lonely Planet recently ranked Ethiopia among the top ten 2017 world tourist destinations,” and that it earned more than $870 million from tourism in the first quarter of 2017 alone. Gathered here are a handful of recent images from across Ethiopia, showing just some of its people and regions.

A priest stands on the edge of a cliff in front of the entrance to Ethiopian Orthodox rock-hewn church of Abuna Yemata Guh in the Gheralta Cluster in the Tigray mountains, on January 28, 2011, in Megab, Ethiopia.

The colorful volcanic landscape of Dallol in Ethiopia’s Danakil Depression, on February 26, 2016.

Portrait of an Afar tribesman with traditional hairstyle, in Assayta, Ethiopia, on March 1, 2016.

Orthodox Christians sit outside the famous monolithic rock-cut churches during a Good Friday celebration in Lalibela, in the Amhara Region of Ethiopia, on May 3, 2013.

A village sits below a prominent hill in the Simien mountain range, near Gondar, Ethiopia, on January 20, 2017.

A woman from the Afar tribe with braided hair and a beaded headband in Chifra, Ethiopia, on January 21, 2017.

The Omo River flows through low lying hills near the Bele Bridge in Ethiopia, on May 18, 2010. The bridge is one of three places along the Omo River’s 472 mile long length where a road reaches it. After rising in the Semien Hills of Northern Ethiopia the Omo ends its journey in Kenya’s Lake Turkana, the world’s largest desert lake. The Lower Omo Valley is home to many unique indigenous tribal peoples that practice flood retreat cultivation in addition to the raising of cattle and goats.

Dean Krakel / Getty

Recently picked wild coffee is dried on a farm outside Bonga, Ethiopia, on December 4, 2012. The Kaffa region is known for its coffee production, wild coffee grown in high altitudes. This region is the original home of the coffee plant, coffee Arabica, which grows in the forest of the highlands. The red berries are the main source of income in the area. Local children and cattle also drink coffee.

Bet Medhane Alem rock church is seen in Lalibela on April 23, 2011. According to legend, angels helped King Lalibela build this church and others like it in the 11th and 12th century after he received an order from God to create a new Jerusalem in Ethiopia.

Portrait of an Ethiopian Orthodox priest holding a cross inside a rock church in Lalibela, in Ethiopia’s Amhara region, on February 23, 2016.

A camel caravan carrying salt mined by hand is led across a salt plain in the Danakil Depression on January 22, 2017 near Dallol, Ethiopia. The depression lies 100 meters below sea level and is one of the hottest and most inhospitable places on Earth.

S0099133317300496A smiling Ethiopian boy named Abushe with striking blue eyes, affected by Waardenburg syndrome (a genetic disorder that can affect pigmentation among other things), in Jinka, Ethiopia, on March 18, 2016.

A smiling woman from the Borana tribe, during an Oromo Gada system ceremony in Yabelo, Ethiopia, on March 6, 2017.

Portrait of an Afar woman with green eyes and tattoos on her face, on January 17, 2017, in Assaita, Ethiopia.

An Ethiopian Orthodox Christian pilgrim is pictured at a mass before the annual festival of Timkat in Lalibela, Ethiopia, on January 19, 2012. Timkat celebrates the Baptism of Jesus in the Jordan River. During Timkat, the Tabot, a model of the Ark of the Covenant is taken out of every Ethiopian church for 24 hours and paraded during a procession in towns across the country.

Carl De Souza / AFP / Getty

A girl from the Suri tribe in Ethiopia’s southern Omo Valley region near Kibbish on September 25, 2016. The Suri are a pastoralist Nilotic ethnic group in Ethiopia. The construction of the Gibe III dam, the third largest hydroelectric plant in Africa, and large areas of very “thirsty” cotton and sugar plantations and factories along the Omo river are impacting heavily on the lives of tribes living in the Omo Valley who depend on the river for their survival and way of life. Human rights groups fear for the future of the tribes if they are forced to scatter, give up traditional ways through loss of land or ability to keep cattle as globalization and development increases.

Stewardesses stand in line during the inauguration of a new train line linking Addis Ababa to the Red Sea state of Djibouti, in Addis Ababa, Ethiopia, on October 5, 2016. #

An aerial view of the El Sod volcanic crater lake where Borana tribesmen dive to collect salt, in Ethiopia’s Oromia Region, on March 4, 2017.

Eric Lafforgue / Art In All Of Us / Corbis via Getty

Ethiopian Orthodox pilgrims jump into the Fasilides baths during the Timkat festival in Gondar on January 19, 2014.

Salt canyons and pillars made of layers of halite and gypsum in the Danakil Depression, near Dallol, Ethiopia, on February 26, 2016.

A girl from the Afar tribe with braided hair, photographed on January 15, 2017, in Afambo, Ethiopia.

The post Beauty and Color: Amazing HD Photos of Ethiopia’s Attractions appeared first on Satenaw: Ethiopian News|Breaking News: Your right to know!.

African Refugee Day in Toronto, Canada

The Honorable Nicola Zingaretti Governor of Lazio Province

$
0
0

                 Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause

           4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044, USA – (214)703 9022

                                   www.globalallianceforethiopia.com

                                                                                          June 2, 2017

The Honorable Nicola Zingaretti

Governor of Lazio Province

Italy.

 

Subject: Removal of Fascist Criminal Rodolfo Graziani’s Mausoleum

The Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause presents its compliments to H.E. Mr. Nicola Zingaretti, Governor of Lazio Region in Italy and submits this appeal for consideration.

It is to be recalled that the Fascist criminal, Rodolfo Graziani, had perpetrated, in his capacity as governor of Ethiopia during the Italian occupation of that country, serious crimes against humanity including the massacre of 30,000 innocent people in only three days (February 19-21, 1937) in Addis Ababa as well as over 2,000 monks and parishioners at the renowned Ethiopian monastery of Debre Libanos. The total number of the Ethiopian people massacred by the Fascists is known to be one million including several young educated Ethiopians trained abroad with the nation’s limited resource. In addition, 2,000 churches, 525,000 homes and 14 million animals were destroyed. It is known that the Fascists used various war materials including the internationally forbidden chemical weapon of mustard gas. It is also well known that Rodolfo Graziani and his Fascist criminals looted huge quantities of Ethiopian properties which have still not be returned. Rodolfo Graziani is also known as “the butcher of Libya” for the massacre that was committed under his leadership.

It was, therefore, with a great deal of astonishment and disappointment that we learned in August, 2012 that a mausoleum was established for the Fascist criminal, Rodolfo Graziani, even as per Italian laws, in the presence of a Vatican representative at the town of Affile.

Your Excellency will recall that we had written a letter of appeal to you dated 16/4/13 and, later, a reminder dated 7/11/15.

It was with a great deal of pleasure and appreciation that we found out from the official bulletin of the Lazio Provincial Authority dated 13/3/15 that it had decided on the removal of the Graziani mausoleum expeditiously as well as the termination of the budget provided for operating the mausoleum failing which legal action would be undertaken. We take this opportunity to express our utmost appreciation and thanks to Your Excellency, the Lazio Provincial Authority and supporters of our cause throughout the world including Italy for the support provided in the quest of removing the Graziani mausoleum.

Although the decision was highly encouraging and an action that was expected from a democratic nation that has a deep respect for justice and human rights, we are deeply concerned that the court case regarding the Graziani mausoleum has been postponed repeatedly to the extent that the prosecution might not achieve the required result.

We understand that the Graziani mausoleum court  case is now due on 11/27/17. We, therefore, appeal to Your Excellency to kindly take the necessary action so that, finally, thanks to God, a verdict for the removal of the mausoleum would be achieved.

With the compliments of our highest consideration,

Yours faithfully,

 

Kidane Alemayehu

Executive Director

 

CC: H.E. Mr. Hailemariam Dessalegn

Prime Minister of Ethiopia.

 

CC: The Ethiopian Embassy in Rome

CC: The Italian Embassy in Ethiopia

CC: The Secretary General

United Nations

New York

 

CC: The African Union

CC: The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church

Addis Ababa

Ethiopia

 

The post The Honorable Nicola Zingaretti Governor of Lazio Province appeared first on Satenaw: Ethiopian News|Breaking News: Your right to know!.

Viewing all 3686 articles
Browse latest View live