Quantcast
Channel: admin – Medrek
Viewing all 3686 articles
Browse latest View live

ለማሳጠር መስራት፤ ስለመርዘምም ማሰብ – ጣሰው አስፋ

$
0
0

ጣሰው አስፋ (tassat@t-online.de)

በፌብርዋሪ 11 እና 12, 2017 በሁለቱ ቀናት ውስጥ በአምስቱም ክፍለ ዓለማት በሚገኙ ከአርባ በላይ በሚሆኑ ከተሞች ለአርበኞች ግንቦት 7 የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የተደረጉ በዓላዊ ዘመቻዎች መካሄዳቸውን የበረታ በየአካባቢ በተደረጉት ዝግጅቶች ላይ በመገኘት ለዓይን ምስክርነት ሲበቃ የተቀረው ኢትዮጵያዊ ደግሞ በሚዲያዎች የታደመው ይመስለኛል።

በዝግጅቱ ላይ ከድጋፍ ማሰባሰቡ በተጓዳኝ  ለአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስካይፔ ከየአካባቢው ጥያቄዎች እየቀረቡ መልስ ሲሰጥም ስለነበር፤ በዚህ አጋጣሚ ከቀረቡት ልዩ ልዩ ጥያቀዌዎች ውስጥ አንድ ሃሳቤን  የሰረቀው ጥያቄ “የትጥቅ ትግሉ በተጠበቀው ፍጥነት አልሄደም” የሚለው ነበር።

ጥያቀው ማንም የባርነት ቀንበር የከበደው ሰብአዊ ፍጡር ሁሉ ሊያነሳው ጥያቄ እንደሆነ የሚያጠያይቅ ኤኢመስለኝም። የመከራና የጭነቀት ጊዜ ሰከንዱ ዘሎ እንደሰዓት፤ ሰዓቱ ተስፈንጥሮ እንደሳምንት፤ ሳምንቱ ወራትን ተሻግሮ ወደመንፈቅ  ወዘተ … እየዘለለ ስለሚርቅ፤ የመከራውን ጊዜ ለማሳጥር  የሚደረገው ሩጫ  መከራው እስከልተገፈፈ ድረስ ፈጥኗል ሊባል የሚችልበት አንዳችም አጋጣሚ አይኖርም። ማጠር መርዘሙ የሚገመገመው ከትግሉ ፍጻሜ በሁዋላ ለመቆየት ዕድል የገጠመው ያለፈበትን የመከራ ጉዞ እያነሳ መወያየት ሲጀምር ነው።

የትጥቅ ትግል የሚመረጠው ይፈጥናል፤ ፈጣን ፈውስ ያመጣል፤ ተብሎ ሳይሆን፤ ሌሎች አማራጮች ሁሉ ተሞክረው ከተገጠመው ክፉ  ባለጋራ አቅም ጋር የሚመጣጠኑ ሆነው ባለመገኘታቸው ምክንያት ብቻ የመጨረሻው አማራጨ ሆኖ የሚወሰድ እነደሆነ መገንዘብ በጣም አስፈላጊ ነው። የእብሪተኞች ጦርነት ኢይደባለቅ።

ከዚያም በተረፈ የትጥቅ ትግልን ጠብመንጃን አንግቦ ሸተት ወደወንዙ ከሚለው አቅጣጫ ብቻ ሳይሆን፤  ከሌሎች ብዙ አቅጣቻዎች ልብ ብሎ ማየት አስፈላጊ ቢሆንም፤ የተነሳሁት ስለትጥቅ ትግል ሰፊ ታሪክና ምሳሌ ለመተረክ ሳይሆን፤ አርበኞች ግንቦ 7ን በተመለከተ ብቻ ጥቂት ማስታወሻ ለማቅረብ ስለሆነ፤ ነገሩ ቀላል እንዲሆን እዚያው አገራችን የተደረጉ የትጥቅ ትግሎችን አንስቼ ቀለል ባለ መንገድ ለሃሳቤ  መቋጠሪያ ላብጅለት።

የኤርትራውያን ነጻ ሃገር ለመሆን የተደረገው የትጥቅ ትግል 30 ዓመት፤ ትግራውያን “ወንድሞቻችን” ደግሞ እኛን በባርነት ለመግዛት የሚያስችላቸውን ነጻነት ለመጎናጸፍ ያደረጉት የትጥቅ ትግል 17 ዓመት ፈጅቷል። ታደያም እነዚህ ሃይሎች የቀደመው ያንድ ትውልድ ዕድሜ ሲያስቆጥር፤ የዃለኛው ደግሞ የዚያን ከግማሽ በላይ ሲያገባድድ፤ ሁለቱም በዚያ ጦርነት ውስጥ መኖር ጥሟቸው፤ ፈጥኖ እንዳያልቅባቸው እየቆጠቡ ያካሄዱት ነበር ብሎ ለማሰብ፤ በዓመታት ለጤነኛ እዕምሮ የሚሞከር አይሆንም።

በደፈጣ ውጊያ ተጀምሮ፤ ወደጨበጣ ጦርነት ተሸጋግሮ ውጤት ለማምጣት የሚደረግ የትጥቅ ትግል መጣል መውደቅ፤ መቅደም መቀደም፤ መግፋት ማፈግፈግ፤ ያገኙትን መልሶ ማጣት፤ ከነጭራሹም ለተወሰኑ ጊዜያቶች ከመስኩ እስከመሰወር  ተመልሶመ መምጣት፤ የሚያደረስ ውጣ ውረድ ያለበት እሩጫ መሆኑን ከጠቀስኳቸው የሁለቱ አማጽያን የትግል ዘመን በመዘገብነው ልምድ በቂ ግንዛቤ እንዳለን ተስፋ ቀደርጋለሁ። ጠቂት ነገሮችን ላክል፤

የትጥቅ ትግሉ የሚካሄድበት ጊዜ፤ ቦታ፤ የውስጥና የውጭ ሁኔታዎች የሚጫወቱትን ሚናም በቅጡ ማጤን ትልቅ ብልህነት  ነው። ለዚህም ከላይ ያነሳዃቸውን ቀደም ሲል በሀገራችን የተደረጉትን ትግሎች እንደምሳሌ ስንወስድ፤ እነዚህ ትገሎች ከየት ነው የጀመሩት? በእነማን መሀከል ሆነው ነበር የሚንቀሳቀሱት?  በእነማን ይደገፉ ነበር? መውጫ መግቢያቸው በየት ነበር? እነዚህን ጥያቄዎች በመመለስ ጊዜ አላጠፋም። መልሱን ከልጅ እሰከ አዋቂ የሚያውቀው ስለሆነ፤ ከዚያ ይልቅ አርበኞች ግንቦት 7 የጠቀስኳቸው አማጽያን የነበራቸው አጋጥሚ አለው  ወይ? ብለን ብንጠይቅና ከመነሻው ብንነሳ፤ መነሻው በስደት የሚኖርበት የባዕድ አገር፤ መውጫ መግቢያውም ይኸው በስደት የሚኖርበት አገር፤ እርዳታም የሚያገኘው ከዚሁ ካስጠጋው ሃገር፤ ይህ ሃገር የሚያደርገው ድጋፍ ደግሞ ለቀደሙት አማጽያን እርዳታ የሚያጎርፉት በዘይት ብር ከናጠጡ መንተግስታት እንደሚገኘው  ዓይነት ሳይሆን፤ ከሚያስተዳድረው ደሃ ሕዝብ ጉሮሮ ተከፍሎ የሚገኝ መሆኑ ሁሉ ተጨማምሮ ሲታይ፤ የአርበኞች ግንቦት 7 ትግል ለፈጣኑም ሆነ ዘግይቶ ለሚመጣው ድል ለመድረስ የሚችለው ነጻነት በናፈቀው ኢትዮጵያዊ ቁርጠኝነት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ግልጽ ይመስለኛል።

ስለዚህም ለዚች ማስታወሻ ምክንያት የሆነኝ “ትግሉ በታሰበው ፍጥነት አልተካሄደም” የሚለውን ነጥብ ያነሱት ሰው ትግሉን በሩቁ ሆነው በታዛቢነት በመመልከት ያነሱት ጥያቄ እንዳልሆነ ስለምገምት፤ የሚያደርጉትን እገዛ አጠናክረው  ይቀጥሉ፤ በዋናነት የሚፈለገው በትግሉ ማመን ነው። የሚደረገው ትግል ዝም አላሉም ለመባል ያህል የሚደረግ ሳይሆን፤ ውሎም ሆነ አድሮ፤ በእርግጥም የባላጋራን አቅም የሚፈትሽ መሆኑን ማረጋገጥ ነው። ስለዚህም እንግዲህ ዛሬ የሚደረገው ማንኛውም ተጨባጭ ስራ ሁሉ አተኩሮው  የመከራውን ጊዜ ለማሳጠር መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ መራዘሙም የትግሉ አካል መሆኑን በሚገባ ማጤኑ፤ በትንሹም በትልቁም ሆደ-ባሻ ሆኖ ተስፋ ከመቁረጥ ያድናል። ይህ አስተሳሰብ አርበኞች ግንቦት 7ን ደጋፊና አባል ብቻ ሳይሆን፤ ማንኛውም ድርጅት ወይም ግለሰብ የነጻነት ታጋይ ሊያጤነው የሚገባ ሂደት ይመስለኛል።

“ዘለዓለም እንደምትኖር ሥራ፤ ነገ እንደምትሞትም አስብ” የሚል ተመክሮ እንዳለ አውቃለሁ፤ አባባሉን ከየት እንደገኘሁት ባላስታውስም። ስለነጻነት ትግሉም “ትግሉን ለማሳጠር ሥራ፤ መርዘም ሊኖር እንደሚችልም አስብ” ቢባል ክፋት አይኖረውም።  በነካ እጄ የሚከተለውን ምራቂ ላድርግና ልሰናበት፤-

ሃሳብ

ከትግሬ ሕዝብ ነጻነት ግንባር የባርነት አገዛዝ ነጻ ለማውጣትና የሁሉም የሆነችዋን ዴሞክራሲያዊ እናት አገራችንን – ኢትዮጵያን – ሊያስረክቡን  ቆርጠው ለመታገል ለተሰለፉ ተቃዋሚ ድርጅቶች ሁሉ ያለኝ መልዕክት፤-

አንደኛ/ የግድ የዚህንና የዚያን ያህል ጊዜ ጠፍቶበት፤ የዚያና የዚህ አስተባባሪነት ታክሎበት የተዋቀረ  የሚለው ትብብር ዓይነት ሳይሆን፤ ምንም ውጣ ውረድ የማያስፈልገው ልታደርጉት የምትችሉት ትብብር እንዳለ ይታለኛል። ይህ ትብብር የሚፈጸመው ተቃዋሚ ድርጅቶቹ ዘረኛውን ስርዓት አስወግዳችሁ የነገይቱን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ አላማቸሁ ያደረጋችሁ እስከሆነ ድረስ፤ አንዱ ጠላትን ለመዋጋት የሚከተለውን የትግል ዘዴ አልቃወመውም ማለት ሳይሆን፤ እደግፋለሁ በማለት ትብብርን ማሳየት፤ አልቃወመውም ማለት ብቻውን፤ ትግሉ በለስ ከቀናው  በውጤቱ አልጎዳም  ከሚል ትርጉም ስለማያልፍ፤ የሚያስከትለው ትዝብት በቀላል የሚታይ አይሆንም።

ሁለተኛ/ በዚህ መደጋገፍ መሃል ደግሞ የሚያጋጭ ነገር ቢፈጠር ግጭቱ የአላማ መዛባትን የሚያሳይ እስካልሆነ ድረስ፤ በምንም ምክንያት በየሚዲያው እየወጡ እንዲህ ሆንኩ፤ እንዲህ ተደረግሁ ማለትን ማቆምና፤ በውስጥ ተነጋግሮ መፍትሄ መስጠት፤

ሶስተኛ/ አንዱ የሚያውቀውና ሌላኛው ያልደረሰበት ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲኖርም፤ ማሳሰቢያውን በውስጥ በማስተላለፍ በሚዲያ ላይ ወጥቶ ሃሌ ማለትን ማቆም። የእነዚህ ዓይነቶቹ ትብብሮች ምንም ዓይነት የተለየ ዝግጅት የማይፈልጉ፤ በአመራሮች መካከል በቴሌፎን ተነጋግሮ የሚጨረሱ ናቸው የሚል ዕምነት አለኝ። የሚጫወቱትንም ሚና ቀላል እንደልሆነ መገንዘቡ ጥበበኝነት ነው። ከዚያ አልፎ በየሜዳው ሃሌ ማለት ግን፤ ለጠላት መዝናኛ ከመሆን አያልፍም።

 

ጥረቴ የታኝን ሃሳብ ከማካፈል አልፎ፤ ትእዛዝ፤ ምክር … ወዘተ የሚል ማንጠልጠያ ተሰጥቶት በምክንያቱ ስራ እንዳትፈቱበት አደራ እላለሁ።

 

መልካም ጊዜ


በደቡብ አፍሪቃ በስደተኞችን ላይ ጥቃት ያደረሱ 100 ግለሰቦች በ24 ሰአታት ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ

$
0
0

ዘርይሁን ሹመቴ

በደቡብ አፍሪቃ ስደተኞችንና የውጨ አገራት ዜጎችን በመቃወም በየካቲት 24ቀን 2017እኤአ በፕሪቶሪያ ጎዳናዎች የተደረገው ሰልፍ በፓሊስ እንዲበተን መደረጉ ተዘግቧል።

ፓሊስ ስደተኞችን በመቃወም የወጡትን ሰልፈኞች አስለቃሽ ጢስና ውሃ በመጠቀም ለመበተን ሙከራ አድርጓል።

ተቃዎሚዎችና ስደተኞች በሁለት ጎራ ተከፍለው ስለት ድንጋይና ዱላ ይዘው ታይተዋል። በህዝቡና በስደተኞቹ መካከል ግጭት እንዳይፈጠር ፓሊስ በዝቅተኛ ከፍታ በሚበር ሂሊኮፍተር ሲቆጣጠር እንደነበረም ታውቋል።

ሰልፈኞቹ የስራ እድሉን ስደተኞች እየወሰዱብን ይገኛሉ በማለት በዋናነት እየከሰሱ ይገኛሉ ። የአገሪቷ ዜጎች ለወንጀል መስፋፋቱ ስደተኞች ላይ ጣታቸውን ቀስረዋል።

የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ህዝቡ በስደተኞች ላያ እየወሰደ ያለውን የአመጽ እርምጃ በጽኑ ኮንነዋል ። በአገሩቱም ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።

አብዛኞች ስደተኞች ህግ አክባሪ እንደሆኑና ለአገሪቱዋም ኢኮኖሚ እድገት አስተዋጸኦ እየደረጉ እንደሆነ ፕሪዝዳንቱ ጨምረው ገልጸዋል።

ሁሉንም ስደተኞች በእጽ ንግድ ወይም በህገወጥ የሰው ዝውውር ተግባር ተሳትፈዋል ብሎ መወንጀል ልክ እንዳልሆነ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ተናግረዋል።

ይልቅ ህዝቡ ንጹሃን ስደተኞችን ከማጥቃት ተቆጥቦ በእንደዚህ አይነት የወንጀል ተግባር የተሳተፉትን እንዲለዩና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ከመንግስት ጋር መተባበር እንዳለበትም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

በፕሪቶሪያ በስደተኞች ላይ እየደረሰ ባለው ጥቃት የጠረጠሩ ከ100 በላይ ግለሰቦችን በ24 ሰአታት ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፓሊስ አሳውቋል።

በደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ወገኖቻችን በዚህ አስጨናቂ ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉ በተለያዩ የአለም አገራት ተሰማርተው የሚገኙ የአባይ ሚዲያ አባላት መልክታቸውን ያስተላልፋሉ።

የወልቃይት ጠገዴ ትግል የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ነው – ዶ/ ር አክሎግ ቢራራ

$
0
0

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ ር) “

የውርደት በትር” ገጽታ “በመጨረሻ እኛ የምናስታውሰው የጠላቶቻችን ቃላቶች ሳይሆን ድምጻቸውን ያጠፉትን የወዳጆቻችን ቸልተኛነት ነው” ዶር ማርቲን ሉዘር ኪንግ

መግቢያ

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ

 

ኢትዮጵያን ለማፈራረስና ሕዝቧን ለእርስ በርስ እልቂት የአመቻቸው የህወሓት፤ ኢህአዴግ አምባገነናዊ ስርአት የፈጠረውን መሰረታዊ ችግር አሁንም ገዢው ፓርቲ አግባብ ባለው ሁኔታ አላየውም፤ ቢያየውም ችግሩን ንቆ ትቶታል። ይህ የጥፋት ክስተት እንዳለ ሆኖ “ተቃዋሚ ነን” የምንለው ግለሰቦችና ስብስቦች በአበይት ብሄራዊ ችግሮች ላይ ምን አይነት አቋም እንወስዳለን? ጥፋቶችን እያየን ለምን ዝም እንላለን? የሚሉት ጥያቄዎች መልስ እንዲሰጥባቸው እጠይቃለሁ።

የእኔ መከራከሪያ ነጥብ እንዲህ የሚል ነው። አማራው፤ ኦሮሞው፤ ጉራጌው፤ አፋሩ፤ አኟኩ፤ ሲዳማው፤ ትግራዩና ሌላው በደሙ መስዋእት ከፍሎ፤ በብሄር፤ በገቢ፤ በጾታ፤ በኃይማኖት ሳይታገድ የኢትዮጵያን ነጻነት፤ ዘላቂ ጥቅምና ሉዐላዊነት ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለእኛና ለተከታታይ ትውልድ ያሸጋገረልንን አገር፤ የኢትዮጵያ ሰፊ ሕዝብ ራሱን አሁንም የትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር (ህወሓት) ብሎ የሚጠራው ጠባብ ብሄርተኛና ፍጹም ጎጠኛ ቡድን ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያችን እንድትበታተንና ሕዝቧ በእርስ በርስ ጦርነት እልቂት እንዲካሄድበት የሚፈቅድ አይመስለኝም የሚል ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአገሩ፤ ለነጻነቱ፤ ለመብቱና ለህይወቱ የታገለው ነጻነቱና ሰብአዊ መብቱ ተከብሮለት በመላው ኢትዮጵያ ለመንቀሳቀስ፤ ለመስራት፤ ለመኖር፤ ኃብት ለማካበት፤ መሪዎቹን ለመምረጥና ለመመረጥ እንዲችል ነው የሚል እምነት አለኝ። በጎሳና በቋንቋ ልዩነቶች ላይ የተመሰረተው የፌደራል ስርዓትና አስተዳደር ይኼን በዜግነት መብቶች አማካይነት ሊሰራ የሚችል የአገር ስርዓት አወቃቀር፤ መንግሥትና አስተዳደር ዋጋ-ቢስ አድርጎታል። ገዢው ፓርቲ፤ በተለይ ህወሓት የዜግነት መብትን

1

ይፈራል፤ የተቀበለውና ስራ ላይ ያዋለው በብሄሮች ልዩነቶች ላይ የተመሰረተ ስርዓትን ነው። ታዲያ ምን ጎደለው?

የተማረከ ስርዓት

ይህ ስርዓት የሚያገለግለው ህወሓትንና ታማኞቹን ብቻ ሆኗል። ወደ ኋላ ዞር ብለን ስንመራመር፤ የኢትዮጵያን ነጻነትና ክብር ስኬታማ ያደረገው አንድ ብሄር አይደለም። ኢትዮጵያ በአንድ ብሄር ተገዝታ አታውቅም። እንዳለመሆኑ መጠን አሁንም አገሪቱን ከጥፋትና ከውርደት የሚነከባከባት አንድ ብሄር አይሆንም። ኢትዮጵያ የሁሉም ብሄረሰቦችና ኃይማኖቶች አገር ናት። በብሄር ተቃርኖ ስልጣን የሚሸምተውና የሚነግደው ህወሓት፤ በብሄረሰቦች እኩለነት አመካኝቶ፤ ሕዝቡን ከፋፍሎ የአንድን አናሳ ብሄር የበላይነት ተቋማዊ አድርጓል።

ለምሳሌ፤ የጋምቤላን ለም መሬት ከነዋሪዎቹ ነጥቆ፤ ለፈረንጆችና ለተመረጡ የትግራይ ተወላጆች አስተላልፎ “እድገት” አካሂዳለሁ ይላል። ይህ እድገት ሳይሆን ውርደት መሆኑን ታዛቢዎች ገምግመውታል። ህወሓት ይህ “ውርደት ነው! አፈና ነው! ኢ- ሰብአዊ መርህ ነው! የባስ ድህነት ነው! ብሎ ትችት የሚያቀርበውን ሁሉ እያደነ ያስራል፤ ይገድላል፤ እንዲሰወር ያደርጋል። የእድገት ትርጉም የተለየ ካልሆነ በስተቀር፤ በኢትዮጵያ ሲካሄድ የቆየው እድገት ለሌቦች፤ ለሙሰኞች፤ በተለይ ለህወሓቶት አመች ሆኖ ቆይቷል። ባለሥልጣናት ችግሩን አይክዱም፤ “ኪራይ ሰብሳቢነት አገር ያጠፋል” ይላሉ። ሌብነት ለማለት ግን አይችሉም፤ አይፈልጉም። “ኪራይ ሰብሳቢነት” እንደ ተራ ነገር ሁሉን አቀፍ የሆነ አባባል ሆኖ ትርጉመ ቢስ ሆኗል። ልክ እንደ “ተሃድሶ” ማለት ነው። እያሰሩና እየሰረቁ “ተሃድሶ” ምን ትርጉም አለው። “ተሃድሶ” ማንን አደሰ’ ማንን አደኸየ?

ቁም ነገሩ ግን፤ አንበሳውን የእድገት ውጤት ማርኮ ራሱን ሃብታም ያደረገው ህወሓት ነው። አዲስ አበባን ተረክቦ ለትግራይ ተወላጆት፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ፤ የከተማ መሬትና ሌላ ግዙፍ ኃብት ለአባላቱና ለደጋፊዎቹ ያስተላለፈው ህወሓት ነው። በአዲስ አበባ ቦሌ “መቀሌ” ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የዚህ የመሬት ነጠቃ፤ የሰፈራና የኢኮኖሚ የበላይነት ውጤት ነው። መሬቱ ከማንና እንዴት እንድተነጠቀ የሚያሳዩ ብዙ መጻጽፍት፤ ምርሞርችና መጻህፍት ስላልሉ አንባቢ ሊከታተላቸው ይገባል። ችግሩ የመረጃ እጥረት አይደለም። በተለይ፤ አስተማማኝ መረጃ ያለው፤ የዱሮው የኢህአዴግ የመገናኛ ባለሥልጣን የነበረው አቶ ኤርምያስ ለገሰ ያሳተመው “የመለስ ልቃቂት” የተባለው መጽሃፍ የህወሓትን ሙሰኛነት፤ ሌብነት፤ ባለጌነት፤ ጠባብ ዘረኛነት፤ ግፍ፤ በደል፤ ኢ-ሰብአዊነት፤ ጸረ- ኢትዮጵያዊነት፤ ጸረ-ሕዝብነት፤ ጸረ-ፍትህነት ወዘተርፈ ጥልቀት፤ ስፋትና አደጋ ቁልጭ አድርጎ አቅርቦታል። ሀወሓት ከሕግ ውጭ የሰበሰበውን ግዙፍ ሃብት አካብቶም፤ እኔ የበላይነቱን ይዠ ካልቆየሁና አሁንም ድርጅታዊ ምዝበራ ለማካሄድ ካልቻኩ አገሪቱ “ትፈራርሳለች” ይለናል። አዲሱ በብሄር ልዩነቶች ላይ የተመሰረተው የፌደራል ስርዓት የቆየውን የሕዝብ ትሥስር አጥፍቶና ልዩነቶችን አጠናክሮ፤ ለአንድ በብሄርህ ለተዋቀረ ድርጅት የበላይነት መሳሪያ ሆኖታል፤ “ለአዲስ የስልጣን ከበርቴዎች” ዋና መሰረት ሆኖ ቆይቷል። ለማጠናከር የምፈልገው ጉዳይ በፖሊሲና በድርጊት ሲታይ፤ ህወሓት የበላይነቱን እስካልያዘ ድረስ ኢትዮጵያ ብትፈራርስና ሕዝቧ እርስ በርሱ ቢተላለቅ ደንታ እንደሌለው ማወቅ የዜግነት ግዴታችን ነው። ይህን መሰረታዊ አስተያየት ለማጠናከር እፈልጋለሁ።

የህወሓት ጽንሰ ሃሳብ መሰረት ህወሓት የተመሰረተውና ስኬታማ ለማድረግ የወሰነው፤ የትግራይን ሕዝብ ለማገልገል ክልሉን “ከኢትዮጵያ ነጻ ማውጣት” ነበር። ምን ተይዞ? በምን የተፈጥሮ ኃብት? የሚለውን ጥያቄ ብናነሳ መልሱ ግልጽ ይሆናል። ከሌሎች የብሄር ስብስቦች ጋር ተመካክሮ ኢህአዴግ የተባለውን ጥምረት የፈጠረበት ዋና ምክንያት ያላሰበውን ኢትዮጵያን በሙሉ ለመግዛት እንዲያመቸው፤ የኢኮኖሚ ጥቅሞችን ለመሰብሰብ እንዲያስችለው፤ መሬቶችን ነጥቆ ለማጠቃለልና የመጨረሻ ግቡን ስኬታማ ለማድረግና ለማመቻቸት እንዲያስችለው ነው። የትግራይ ክልል ገና ባይገነጠልም፤ ይህ ህወሓት ሲመሰረት የጸነሰው የመሬት ነጠቃና የመስፋፋት እቅድ ተሳክቶለታል።

በአገር ደረጃ ሲታይ፤ ዘጠና ዘጠኝ በመቶ የሚገመተው ህገ ወጥ “ኪራይ” የተሰበሰበው ከትግራይ ክልል ውጭ ነው። ለምሳሌ ከአዲስ አበባ፤ ከኦሮሞያ፤ ከደቡብ፤ ከአማራ። ለም መሬቶቹና ወንዞቹ የተነጠቁት የሌላው ሕዝብ የተፈጥሮ ኃብት ነው። የፖለቲካ የበላይነቱ ለህወሓትና ለደጋፊዎቹ የጠቀመው ለዚህ “ኪራይ ሰብሳቤነትና” የግልና የቡድን ኃብት አካባችነት ሆኗል። ግዙፍ ስልጣን! ግዙፍ ኃብት! አስገኝቷል። ሌሎቻችን ይህን የፖለቲካ ስልጣን የበላይነት ከኢኮኖሚና ከተፈጥሮ ኃብት የበላይነት ጋር ማያያዝ አለብን የሚል እምነት አለኝ። ምክንያቱም፤ በክልሎች የሚካሄደው ግፍ፤ በደልና ድርጅታዊ ምዝበራ በአገር አቀፍ ከሚካሄደው እምብዛም አይለይም። የሚዘረፍበትን ቦታ የሚወሰነው የሚሰጠው ጥቅም ነው።

PDF- ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ብአዴን አከርካሪው ላይ ተቆርጧል – ሕዝብ እነ ደመቀን “በቃችሁ” አላቸው!

$
0
0
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ወደ ጎንደር አቅንተዉ ነበር፡፡ በደመቀ መኮንንና በገዱ አንዳርጋቸዉ የተመራዉ ከፍተኛ አመራር ቡድን ሦስት ዋናዋና ቁልፍ ተልዕዎኮችን ለማሳካት ከባህርዳር እንደተንቀሳቀሰ የጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ የብአዴን ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡ አንደኛ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የመራዘሙን አስፈላጊነት ለህዝብ ለማሳመን፤ ሁለተኛ የነጻነት ኃይሎች በሀገር ሽማግሌዎች አደራዳሪነት ከአገዛዙ ጋር ዕርቅ እንዲያወርዱ ከሚያስችሉ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ለመምከር፤ በሦስተኛ ደረጃ የተያዘዉ ተልዕኮ አብይ ጾምን ምክንያት በማድረግ በአማራና በትግራይ ህዝብ መካከል የተፈጠረዉን ቅራኔ በኃይማኖት አባቶች የምኩራብ ስብከት አማካይነት እንዲበርድ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አቅጣጫ በሰሜን ጎንደር ዞን ሀገረ-ስብከት ሥር ላሉ አድባራት በአቡነ ኤልሳዕ በኩል መልዕክቱን ማድረስ የሚሉት ሦስት ጉዳዮች የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ወሳኝ ተልዕኮዎች ነበሩ፡፡

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በህወሓት/ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ተገምግሞ አዋጁ በመሀል አገር፣ በደቡብና በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል እንደወትሮዉ ሁሉ አንጻራዊ ሰላም ቢሰፍንም፤ በሰሜን ምዕራብና በኦሮሚያ ከፊል ቦታዎች ሠላምና መረጋጋቱ በአደባባይ የሰፈነ ቢመስልም በሥራ አስፈጻሚዉ ግምገማ   “አስተማማኝ” አለመሆኑ ታምኖበታል፡፡ በተለይም በሁለቱም ግዙፍ ክልሎች የጦር መሳሪያ ዝዉዉሩ እየጨመረ መሄዱ፤ በጎበዝ አለቆች የሚመሩ ቡድኖች እዚህም እዚያም ከህወሃት/ኢህአዴግ ኃይሎች ጋር የደፈጣ ዉጊያ የሚያካሂዱ በመሆኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለተጨማሪ ሦስት ወራት እንዲራዘም መደረጉ ይነገራል፡፡

ይህንን የህወሓት/ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ወሳኔ “በህዝብ ዉይይት” እንደዳበረና ይሁንታ እንደተሠጠ ለማስመሰል በጎንደር ከተማ “ህዝባዊ ስብሰባ” እንደተጠራ የሚገልጹት የጎልጉል የመረጃ ምንጮች፤ ስብሰባዉ የሰሜን ጎንደር ዞን ብአዴን ጽ/ቤት አዳራሽ የካቲት 13/2009ዓ.ም ረፋድ 4፡00 ሠዓት ላይ በብአዴን ከፍተኛ አመራሮች መሪነት ተካሂዷል፡፡

በስብሰባዉ ላይ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የዕርድ፣ ማህበራትና አደረጃጀት አመራሮች፣የሙያ ማህበር ተወካዮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተማ የብአዴን መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

በደመቀ መኮንን ንግግር የተከፈተዉ ይሄዉ ስብሰባ ገና ከጅምሩ የአጀንዳ መስመሩን የለቀቀ ነበር፡፡ “የጋለ ህዝባዊ ስሜት የተንጸባረቀበት ስብሰባ” እንደሆነ የሚጠቁሙት የመረጃ አቀባዮች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የመራዘሙን ጉዳይ በተመለከተ በስብሰባዉ ላይ የተገኙ አንድ የአገር ሽማግሌ የሰጡት አስተያየት የተሰብሳቢዎችን ልብ የነካ ነበር፤ “የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አነሳችሁት አላነሳችሁት ጎዳናዉ ላይ በጥይት የወደቁ ልጆቻችን ህይወት አይመልስም፤ እናንተም መግደላችሁን ላታቆሙ ለምን ታባብሉናላችሁ?” ያሉት የአገር ሽማግሌዉ ንግራቸዉን ሲጨርሱ “የደርግን መጨረሻ ማስታወስ ብልህነት ነዉ” ሲሉ ምክር አዘል ማስጠንቀቂያ ለግሰዋል፡፡

ከንግዱ ማህበረሰብ ተወክለዉ የተገኙት ታዋቂዉ የባህል ልብስ ነጋዴ ሐጅ ሐሰን አሊ “የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከል የሆነዉ ቅዳሜ ገበያ ምክንያቱ ዛሬም ድረስ ባልተገለጸልን ሁኔታ 446 ሱቆች በእሳት ቃጠሎ ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል፡፡ በዚህ የተበሳጨ ነጋዴ ራሱን እንዳጠፋ እኔና የአካባቢዉ ሰዎች ምስክሮች ነን፤ ትዳር ፈርሷል፤ ልጆች ተበትነዋል፤ ጎንደር በቴሌቪዥን ዜና እንደሚነገርላት የተረጋጋች ከተማ አይደለችም፤ ማህበራዊ ቀዉሱ የከፋ ነዉ፤ ይሄን መላ ካላላችሁ ምኑ ላይ ነዉ መንግስትነታችሁ?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ከኃይማኖት አባቶች ተወክለዉ ከተገኙት መካከል የፊት አቦ አቡነ አረጋዊ ደብር አለቃ የሆኑት አለቃ መኮንን ወልዱ በበኩላቸዉ “አሁን በልዑል እግዚአብሔር ሥም አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ጎንደር በታሪኳ በደርቡሽ ወረራ ጊዜ አንድ ዘመን ብቻ ብርሃነ መስቀሉን በአደባባይ አላከበረችም፡፡ ከስንት እና ስንት ዘመናት በኋላ ዘንድሮ ጎንደር ላይ የመስቀል በዓል በአደባይ ሳይከበር ቀረ፡፡ እናስ እናንተን ከወራሪዉ ደርቡሽ ለይቶ ማየት ብንቸገር ትፈርዱብን ይሆን? የጥምቀት በዓልስ ቢሆን ከካህናቱ መስቀል በላይ ጠመንጃ አንጋቹ በዝቶብን ለክርስቶስ ከብር ዝቅ ብለን በዓለ ጥምቀቱን አከበርን፡፡ ሌላዉ ቢቀር አላፊ ነን ብላችሁ እንዴት ማሰብ ተሳናችሁ? ሁላችንም ስናልፍ የምንቀበርባትን ቤተክርስቲያን እንዲህ ፈተና ማብዛት በጎ አይደለም ልጆቼ” በማለት አባታዊ ግሳጼ እንደሰጡ የጎልጉል መረጃ ምንጮች ዘግበዋል፡፡

ስብሰባዉ በተደጋጋሚ “አካሄድ፣ ሥነ-ሥርዓት…” በሚሉ ቃላት በተደጋጋሚ ይቋረጥ እንደነበር የገለጹት ምንጮች የብአዴን መካከለኛ አመራሮች ተመሳሳይ ይዘት ያላቸዉን ጥያቄዎች ለከፍተኛ አመራሩ አቅርበዋል፡፡

በተለይም ህዝባዊ አመጹ ከተነሳ ወዲህ ከመስከረም እስከ ጥር ድረስ በከተማዉ አራት መቶ ሃያ ስድስት ባዶ ቦታዎች የጨረቃ ቤት እንደተሰራባቸዉ፤ የሀሰት የሥም ንብረት ዝዉዉር በዉልና ማስረጃ በኩል እየተፈጸመ እንደሆነ፤ ከመንግስትና ከግል ተቀጣሪዎች ከሚሰበሰበዉ የገቢ ግብር ዉጪ የንግድ ግብር ይህ ነዉ በሚባል ደረጃ እንዳልተሰበሰበ፤ ሆቴሎች በቱሪስት እጦት ሠራተኞቻቸዉን ለመቀነስ እንደተገደዱ፤ ወዘተ የመሳሰሉ ችግሮች በከፍለ ከተማና በከተማ አስተዳደሩ መካከለኛ አመራሮች በኩል “ከአቅም በላይ” ሆነዋል በሚል ለከፍተኛ አመራሩ ተጠይቋል፡፡

“ይህ ሁሉ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግር ሲደርስ አመራሩ የት ነበር?” የሚል ኃይለ ቃል የተናገረዉ ደመቀ መኮንን ሰሚ አልባ ስብከቱን ሲያሰማ እንደዋለ የምንጮቻችን ዘገባ ይጠቁማል፡፡

ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ ያለዉን ጉዳይ፤ የአማራና የትግራይ ክልል ድንበር ማካለል ጉዳይ በተለይም የግጨዉ መሬት ጉዳይ አንዲሁም በእስር ላይ ያሉትን የማንነት ጥያቄ አስተባባሪዎችን የተመለከቱ ጥያቄዎች በስብሰባዉ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ የተነሱ ነበሩ፡፡

“የወልቃይት ጉዳይ በህዝበ ዉሳኔ እንዲወሰን የፌደራሉ መንግስት ከትግራይ ክልል ጋር በመተባበር በቅርቡ እንቅስቃሴ ይጀመራል፡፡ የክልል ድንበር ማካለሉን ጉዳይ እንደ ድርጅትም እንደ ክልልም በጋራ ለመስራት ሥራዎች ተጀምረዋል” ያለዉ ደመቀ መኮንን ንግግሩ በስብሰባዉ ተሳታፊዎች ጩኸት በተደጋጋሚ ለማቋረጥ ተገድዷል፡፡

“ህዝቡ እየጠየቀ ያለዉ እናንተ እንድትወርዱ ነዉ እንጂ የወልቃይት ጉዳይ በህዝበ ዉሳኔ እንዲፈታለት አይደለም፡፡ ደግሞስ የፌዴራሉ መንግስትና የትግራይ ክልል ምንድነዉ ልዩነታቸዉ? አማራነት በህዝበ ዉሳኔ አይነጠቅምም፤አይገኝምም” በሚሉ ኃይለ ቃላት ተቃዉሞዉን ያሰማዉ ወጣት ደሳለኝ ኃይሉ ከስብሰባዉ መጠናቀቅ በኋላ ምሽት 3፡00 ሠዓት ላይ ከመኖሪያቤቱ “በኮማንድ ፖስቱ ትፈለጋለህ” በሚል እንደተወሰደ የጎልጉል የአካባቢዉ ምንጮች አአስታውቀዋል፡፡

ስምምነት በሌለዉ መልኩ በተጠናቀቀዉ ስብሰባ፤ ተሳታፊዎች ባይቀበሉትም የሚከተሉት ዉሳኔዎች በከፍተኛ አመራሩ ለተሰብሳቢዎች ተገልጸዋል፡፡

አንደኛ የጎንደርና አካባቢዉ ሠላም በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመጋቢት 28/2009 አስከ ሰኔ28/2009 ድረስ ለተጨማሪ ሦስት ወራት እንደሚቀጥል፤

ሁለተኛ በየአካባቢዉ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የከተማዋና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ፣ የህገ ወጥ የጦር ማሳሪያ ዝዉዉር ለአካባቢዉ አለመረጋጋት የስጋት ምንጭ በመሆኑ በጋራ እንዲከላከሉ፤

ሦስተኛ የጎንደርና አካባቢዉ ህዝብ ከትግራይ ጋር ሠላማዊ ግንኙነት እንዲኖረዉ ይህንንም የኃይማኖት አባቶች ኃላፊነት እንዳለባቸዉ ተማጽኖ አዘል ዉሳኔ በንባብ አሰምተዋል፡፡

ገዱ አንዳርጋቸዉ በቀሰስተኝነት ስሜት “አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድማማች ህዝቦች…” የሚሉ ቃላትን እየደጋገመ ሲጠቀም በተስተዋለበት ስብሰባ፤የደመቀ መኮንን ንግግር በአንጻሩ ተደጋጋሚነት ባለዉ መልኩ በስብሰባዉ ታዳሚዎች ተቋርጧል፡፡ ይህም “የብአዴን መካከለኛ አመራሮች ከከፍተኛ አመራሩ ጋር ተናብበዉ መስራት እንዳቃታቸዉና የመዋቅር መሽመድመድ የታየበት የሽንፈት ስብሰባ ነበር” ሲሉ ስብሰባውን የተከታተሉ አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል፡፡ ሁኔታውን ሥር ከሰደደ የአመራር ክሽፈት አንጻር የሚመለከቱ ግን “እነ ደመቀ በቅቷቸዋል፤ ብአዴን ደግሞ እንደ ድርጅት አከርካሪው ላይ ተቆርጧል” በማለት በመካከለኛና በከፍተኛ አመራሩ መካከል ያለውን ከፍተኛ አለመናበብ እንደ ማስረጃ ያቀርባሉ፡፡

የጎንደሩ ህዝባዊ አመጽ ተራዛሚነት በጦር መሳሪያ ለማስቀጠል ከሚተጉ የነጻነት ኃይሎች መካከል በወገራ በኩል በተለይም አጅሬ፣ አምባ ጊዮርጊስና አንቃሽ አካባቢ ያሉት የነጻነት ኃይሎች በህዝቡ ጥላ ስር ታቅፈዉ ጥቃት ከማድረስ አልቦዘኑም፡፡ የነጻነት ኃይሎችን እንቅስቃሴ ለመግታት ሽምግልናና ዕርቅን ጨምሮ ረዘም ያለ መንገድ ለመጓዝ የሞከሩት የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ሙከራቸዉ በተደጋጋሚ ከሽፏል፡፡ “ዕርቅና ሠላም የተባለው ሙከራ ከጀርባዉ ያዘለዉን ሸፍጥና ሴራ ቀድመዉ የተረዱት የነጻነት ኃይሎች ለሽምግልና የላኳቸዉ ሰዎች በተደጋጋሚ ተመልሰዋል” የሚሉ ወገኖች “የነጻነት ኃይሎች በራቸዉ ለዕርቅ ዝግ ነዉ” ሲሉ አስተያየታቸዉን ለጎልጉል ሰጥተዋል፡፡

“የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እንደ ገና ዳቦ ከላይም ከታችም እሳት እየፈጃቸዉ ነዉ፡፡ ከላይ የህወሓት የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮች ጫና ከታች በኩል ደግሞ የህዝብ ዓይናችሁን ላፈር ባይነት በግልጽ ይታያል” የሚሉት ሌላኛዉ የጎልጉል አስተያየት ሰጪ “እሳቱን ለማጥፋት ብቸኛ አማራጭ ህዝባዊ ዝንባሌ ማሳየት” መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ሲቀጥሉም፤ “ዞረም ቀረም የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እንደ ድርጅትም ሆነ እንደ ክልል እየመጣባቸዉ ያለዉን ህዝባዊ ተቃዉሞ ማስተንፈስ አልቻሉም፡፡ መካከለኛ አመራሮችም የግርግር ክፍተቶችን ተጠቅመዉ በመሬት ወረራ፣ በሀሰት ሥም ንብረት ዝዉዉርና በቀረጥና ግብር ተመን ላይ ይፋዊ ቅርምት ዉስጥ እንደ ገቡ እርስ በርሱ በሚጣረስ መልኩ በስብሰባዉ ላይ “ከአቅም በላይ ችግር” በሚል በራሳቸዉ አንደበት የራሳቸዉን ገመና መግለጻቸው የእነርሱን አለማፈር ብቻ ሳይሆን ድርጅቱ የማይወጣበት ቅርቃር ውስጥ መግባቱን” ያሳያል ብለዋል፡፡

የብአዴን የመዋቅር ወገብ እየተቆረጠ ለመሆኑ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮችን እንደ ማሳያ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ድርጅቱ “የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ የሥርዓቱ ጠንቅ ነዉ፤ በጋራ ልንታገለዉ ይገባል” በሚል መዋቅራዊ መሽመድመዱን ለመሸፋፈን ቢሞክርም ህዝብ ፊት እንደ ብአዴን፤ ድርጅታዊ አቋምን ማሳየት እንደ ተሳናቸዉ የጎንደሩ ስብሰባ አስረጅ ምሳሌ ነዉ፡፡

“እነዚህን የታሪክ አተላዎች ሙሉ በሙሉ ነቃቅሎ ለመጣል ጊዜዉ አሁን ነዉ” በሚሉና “የለም የብአዴንን መካከለኛ አመራሮችን አቅም ከነ መዋቅሩ ወደ ህዝባዊ ዝንባሌ መቀየር ይቻላል” በሚል ተስፋ ከመካከለኛ አመራሮች ጋር ግንኙነት መፍጠር የጀመሩ ወገኖች መኖራቸዉን የጎልጉል የመረጃ ምንጭ ዘገባ ያመለክታል፡፡

በወታደራዊ ዉጥረት ዉስጥ የምትገኘዉ ጎንደር ከተማ እንደተለመደዉ የብአዴን ከፍተኛ አመራሮችን አሸማቃ አሰናብታለች፡፡ የህወሓት የበቀል ጅራፍ አብዝቶ የሚጎበኛት ጎንደር ጊዜ የሚነግረን ሀቅ ቢኖርም በእስካሁኑ ሂደት መከራዋን መሻገር ተስኗታል፡፡ እንደ ጎልጉል የመረጃ ምንጭ ነዋሪዎቿም ለአደባባዩ አመጽ ዝግጁ ይመስላሉ፡፡ ዳግማዊዉ አመጽ በቅርብ ጊዜ የሚፈጠር ከሆነ አመጹ በቀላሉ እንደማይገታ ይገመታል፡፡ ምናልባትም አመጹ እስከ እርስ በርስ ጦርነት እንደሚደርስ አስተያየት ሰጪዎች ስጋታቸዉን ይጠቁማሉ፡፡ የብአዴን አከርካሪ መቆረጥ ከኦህዴድ ተመሳሳይ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ ከፍ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ ከተቻለ ህወሓትን ኅልውና እንደሚያሳጣው በብዙዎች ዘንድ ይታመናል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”

Ethiopia: Arena Tigray must convert itself into a national party – nazret.com

$
0
0

There is no website configured at this address.

You are seeing this page because there is nothing configured for the site you have requested.
If you think you are seeing this page in error, please contact the site administrator or datacenter
responsible for this site.

Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”

የእማሆይ ነገር ! – ይድነቃቸው ከበደ

$
0
0

አንዲት መነኩሴ በታላቁ ኩዳዴ ጾም እንቁላል ያምራቸውና ፣ አንድ እንቁላል ይዘው ከገዳማቸው ወጣ ወዳ አለ ስፍራ ይሄዱሉ፡፡ የጋለ ድንጋይ ፈልገው እንቁላሉን ድንጋዩ ላይ ያፈርጡታል ።ብዙም ሳይቆይ፤ አንድ የገዳም አባት በዛ በኩል ለጉዳይ ብቅ ሲሉ፤ እማሆይ ድንጋይ ላይ እንቁላል ለመጥበስ ፀሀይን እና ድንጋይን ለማገናኘት ሲባክኑ ያገኙዋቸዋል፡፡ የገዳሙ አባት መነኩሴዎን ምነው እማሆይ ? ቢሏቸው “ሠይጣን አሳስቶኝ” ሲሉ። ሠይጣንም ቁጭ ብሎ ከእሟሆይ ሙያ እየተማረ ነበርና ብሽቅ ብሎት፤ “ የእውነት ይህን ዓይነት እንቁላል አጠባበስ ያለዛሬም አላዩሁት አለ” ይባላል፡፡

የማይገባንን ግን የምንፈልገውን ለማግኘት ደፋ ቀና ስንል፣ ለማይገባን ነገር መባከናችንን ታዝቦ ፤ እንዴትስ ይሆናል ? ብሎ ለሚጠይቀ የምንፈጥረው ሰበብ እና አላስፈላጊ ምክንያት ፤ መቼም ማለቂያ የለውም ። ምን ይሄ ብቻ የምንፈጥረው ሰበብ ወይም ምክንያት ፤ ሰበብ ወይም ምክንያት የምናደርገው ነገር ተሰምቶ ፣ ታይቶ የማይታወቅ ምን አልባትም ወደፊትም የማይኖር ጭምር ሊሆን ይችላል ። እማሆይ ሊበሉት ያሰብት እንቁላል ከምንም በላይ ደግሞ ያጠባበስ ዘዴያቸው ፤ እማሆይ ሰበብ ያደረጉት ሰበበኛው እራሱ አያውቀውም ፤ እንዳሁኹም ሰበበኛው ሰይጣን ቁጭ ብሎ ከእማሆይ ሙያ እየተማረ ነበር ። እሱም “ የእውነት ይህን ዓይነት እንቁላል አጠባበስ ያለዛሬም አላዩሁት አለ መባሉ ለዚህም አይደለ ። ሰኔ እና ሰኞ አይነት ሆነና ነገሩ ፣ ይህ ጽሁፍ እና የእማሆይ ነገር ! በኩዳዴ ጾም ገጠመ።


ከሰሞኑ የሚፃፈው ፣የሚወራው ለጉድ ነው። አንዱ ሌላውን ለመደገፈ እና ለመቃወም የሚወረወረው የነገር አንካሴ ፣የወርዋሪው ልክ-የለሽ ድፍረት ፍንትው አድርጎ የሚያስይ ነው። የራስ የሆነውን ነውርን ለሌላው ለመስጠት የምናመካኘው ሰበቡ ሲታይ ፣ እዚህ ላይ ፈጣሪ ጠብቀኝ የሚያስብል ነው ። ሌላውን መስደብ እና ማዋረድ፣ የተሳዳቢውን ጨዋነት የሚያረጋግጥ የሚመመስለን በዝተን መታየታችን አይጣል ነው። ይበልጥ ደግሞ ሰለ-ሚባለው ነገር ፣ ግራ ቀኙን መዝኖ የራስ የሆነ አቋም ለመያዝ ከመሞከር ይልቅ ፤ “ወሬ ሲንግሩህ ሃሳብ ጨምርበት” ይሉት አይነት ነገር ፣ ይሄን ሰሞን ወዲህ እና ወዲያ የሳይበር (የማህበራዊ ድረ-ገጽ) እና የመገናኛ ብዙሃን ሹኩቻው ለጉድ ነው።

ልብ ያልን እንደሆነ ፤ሰዎች ስለሌላው ጥሩ ነገር ሲነግሩን ፣ ደግመን ደጋግመን ማረጋገጫ እንፈልጋለ። ከዚያም የዛ ሰውን ጥሩነት ወይም ስኬት ቀስ ብለን ማንሻኮክ ሥራ ሆኖብን ምንዳ እንጠብቃለን ። ሆኖም ግን አንዱ ስለ ሌላው መጥፎነት ሲነግረን ምን አይነት ማረጋገጫ ሳያስፈልገን ፤ “ወሬ ሲነግሩህ ሃሳብ ጨምርበት” እንደሚባለው የራሳችንን ግምት ጨምረንበት ፍጽም ከእውነት የራቀውን የሐሰት ወሬ በመጮህ ለማሰማት እንሞክራለን ። ይህም አልበቃ ብሎን ለመቅበር ጉድጎድ እንምሳለን፣ በቆፈርነው ጉድጎዳ ማን ይቅደም ሳናውቅ። ይህ ሁሉ የአብዛኞቻችን ችግር ነው። ለዚህም የሚሻለው በጎ ልቦና ፈጣሪ እንዲሰጠን መጸለይ እና እራስንም ለበጎ ነገር ማትጋት ነው።

በጎ ልቦና ይታገሳል፣ በጎ ልቦና ይቅር ባይ ነው፣ በጎ ልቦና የተከለከለ እና የተፈቀደን ለይቶ ያመላክታል፣ በጎ ልቦና በእራስ ላይ እንዲሆን የማይፈለግ በሌላው ላይ እንዳይሆን ያስጠነቅቃል፣ በጎ ልቦና የወደቅውን ለማንሳት እንጂ የቆመውን ለመጣል አይባዝንም፣ በጎ ልቦና ለስህተት ሣይሆን ከስህተት ለመውጣት ምክንያት ይፈልጋል፣በጎ ልቦና ትላንት፣ዛሬ እና ነገን ያስባል፣ በጎ ልቦና ከፀብ እና ከሐሜት ይልቅ ፍቅርን ፣ሰላምን እና ተግሳጽን ያስቀድማል ፣ በጎ ልቦና የእማሆይ ነገር አስታውሶ ከሰበብ ይጠብቀናል። ምን ይሄ ብቻ ከዚህ በላይ የሆነውን ለማሰብና ለማድረግ የበጎ ልቦና አሰተዋአዖኦ ቀላል አይደለም ። እናም ፈጣሪ በጎ ልቦና ይስጠን፤ አሜን!!!

(ይድነቃቸው ከበደ)

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር፤ አሜን!!!


የማይፈራና የማይሸማቀቅ ታላቅ ሕዝብ – የሚሊዮኖች ድምጽ

$
0
0

ም/ጠ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን እና አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በጎንደር ሕዝቡን ሰብሰበው ማነጋገራቸው የሚታወቅ ነው። ጎልጉል በስብሰባው ከሕዝቡ ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል የተወሰኑትን ለአንባቢያኑ አቅርቧል።

ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል የሚከተሉትን አቅርበናል። አቶ ደመቀና አቶ ገዱ በርካታና በትህትና ሕዝቡን ለማነጋገር መዘጋጀታቸውን በአዎንታዊነት ሊወስድ የሚገባው ነገር ነው። አመራሮች በዚህ እመልኩ የሕዝቡን ስሜት መገንዘባቸው ምን አልባትም በዉስጥ ኢሓዴግ አመራሮች ስብሰባ ላይ ልፍስፍ ሳይሆን ጠንካራ ሆነው ሊወጡ የሚችሉበትን ሁኔታ ሊፈጥርላቸው ይችል ይሆናል። ህዝብ ያን ያህል አክብሯቸው በሰብሰባቸው ተገኝቶ ያለዉን ፍላጎት ገልጾላቸው ፣ እነርሱ ግን ሕዝብን ከማዳመጥና ሕዝብን ከማገለገል የነ አባይ ወልዱና የነ ስህተ ነጋ አሽከር መሆን ከፈለጉ፣ ከሕዝቡም ከሕወሃቶች ሳይሆን ሜዳ ላይ ተጥለው የሚቀሩ ነው የሚሆኑት። ሕወሃት በባዴን ላይ (አመራሮቹንም ሳይቀር) ጥርስ ነቅሷል። በጎንደር እንዳደረጉት ሕዝቡን ለማናገር መሞከራቸው ፣ ሕዝቡም የተሰማዉን እንዲናግቀር መፍቀዳቸው ፣ በራሱ ሕወሃቶችን የሚያናዳድ ነው። ሕወሃቶች ሕዝብ ሲዋረድም ሲሸበር እንጅ ህዝብ ሲከበር አይወዱምና።

የጎንደር ህዝብም ምን እንኳን የአጋዚ በትር በሚሰቀጠጥ ሁኔታ ቢያርፍበትም፣ ቀን ብሎ ከመሄድ የተገታበት ሁኔታ የለም።፡ ኮምንድ ፖስትና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጎንደርን አንገት አልስደፋም። የጎንደር ሕዝብ በድፍረትን በወኔ ነበር አስተያየቱን በስብሰባው ላይ ሲሰጥ የነበረ።

ከተሰጡ አስተያየቲች መካከል ጥቂቶቹ እንሆ፡

አንድ የከተማዋ ነዋሪ
“የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አነሳችሁት አላነሳችሁት ጎዳናዉ ላይ በጥይት የወደቁ ልጆቻችን ህይወት አይመልስም፤ እናንተም መግደላችሁን ላታቆሙ ለምን ታባብሉናላችሁ?” ያሉት የአገር ሽማግሌዉ ንግራቸዉን ሲጨርሱ “የደርግን መጨረሻ ማስታወስ ብልህነት ነዉ” ሲሉ ምክር አዘል ማስጠንቀቂያ ለግሰዋል፡፡

ታዋቂዉ የባህል ልብስ ነጋዴ ሐጅ ሐሰን አሊ፡
“የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከል የሆነዉ ቅዳሜ ገበያ ምክንያቱ ዛሬም ድረስ ባልተገለጸልን ሁኔታ 446 ሱቆች በእሳት ቃጠሎ ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል፡፡ በዚህ የተበሳጨ ነጋዴ ራሱን እንዳጠፋ እኔና የአካባቢዉ ሰዎች ምስክሮች ነን፤ ትዳር ፈርሷል፤ ልጆች ተበትነዋል፤ ጎንደር በቴሌቪዥን ዜና እንደሚነገርላት የተረጋጋች ከተማ አይደለችም፤ ማህበራዊ ቀዉሱ የከፋ ነዉ፤ ይሄን መላ ካላላችሁ ምኑ ላይ ነዉ መንግስትነታችሁ?”

የፊት አቦ አቡነ አረጋዊ ደብር አለቃ የሆኑት አለቃ መኮንን ወልዱ ፡
“አሁን በልዑል እግዚአብሔር ሥም አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ጎንደር በታሪኳ በደርቡሽ ወረራ ጊዜ አንድ ዘመን ብቻ ብርሃነ መስቀሉን በአደባባይ አላከበረችም፡፡ ከስንት እና ስንት ዘመናት በኋላ ዘንድሮ ጎንደር ላይ የመስቀል በዓል በአደባይ ሳይከበር ቀረ፡፡ እናስ እናንተን ከወራሪዉ ደርቡሽ ለይቶ ማየት ብንቸገር ትፈርዱብን ይሆን? የጥምቀት በዓልስ ቢሆን ከካህናቱ መስቀል በላይ ጠመንጃ አንጋቹ በዝቶብን ለክርስቶስ ከብር ዝቅ ብለን በዓለ ጥምቀቱን አከበርን፡፡ ሌላዉ ቢቀር አላፊ ነን ብላችሁ እንዴት ማሰብ ተሳናችሁ? ሁላችንም ስናልፍ “የምንቀበርባትን ቤተክርስቲያን እንዲህ ፈተና ማብዛት በጎ አይደለም ልጆቼ”

የብአዴን መካከለኛ አመራሮች ተመሳሳይ ይዘት ያላቸዉን ጥያቄዎች ለከፍተኛ አመራሩ አቅርበዋል፡፡እነ ደመቀ ከሕዝቡ ፣ ከባዴን መካከለኛና ታችኛው አመራር ዉጭ ለመሆን ከሞከሩ ዘንዶ በአንገታቸው ላይ ጠመጠሙ ማለት ነው።

ፍረጃን የስህተት መሸፈኛ ያደረገው የተቃውሞ ጎራ (ምላሽ ለኢንጂነር ይልቃል) – ግሬስ አባተ

$
0
0

ኢ/ር ይልቃል ከSBS Amharic ጋር ያደረጉትን ቆይታ አደመጥኩት፤ በከዚህ ቀደም ፅሁፌ እንዳልኩት ‹በኢትዮጵያ የተቃውሞ ጎራ ፖለቲካ ውስጥ ለሚሰሩ ስህተቶች ሌሎችን ‹‹ወያኔ›› ማለት እራስን ከስህተት ነፃ የሚያድርግ ነው፡፡ ኢ/ር ይልቃል 22 ደቂቃዎችን በፈጀው ቆይታቸው ሌላው ሁሉ ቀርቶ በመሪነታቸው የነበራቸውን መድረኮች በመጠቀም ችግሮችን ለምን መፍታት እንዳልቻሉ እንኳ ትንፍሽ ሳይሉ ሌሎችን በባንዳነት መፈረጅ መርጠዋል፡፡ ይህ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ የፓርቲው የስነስርአት ኮሚቴ እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች አራት አባላትን የመጠየቅ አቅም መፍጠሩ በአፍራሽነት ነው ያስፈረጀው፡፡


ይህን አሮጌ የፍረጃ ፖለቲካ የሙጥኝ ብለው በዛው አንደበታቸው እንዲህ ይላሉ ‹‹ዋና ከምላቸው የሰማያዊ ፓርቲ አስተዋፅኦዎች ይህን ትውልድ ከ60ዎቹ ትውልድ ፖለቲካ አላቆ አዲስ እርሾ እንዲሆን አድርጓል›› ከዚህ በላይ ፌዝ የለም፡፡ ቁምነገሩ እኮ የተዋናዮቹ የእድሜ ለውጥ አይደለም፡፡ የአስተሳሰብና የተግባር ነው፡፡ ዛሬም ተቀናቃኝ የሆነውን አካል በጠላትነት እያዩ፣የሃሳብ ልዩነትን ከፍረጃ ተሻግረው ማስተናገድ እንኳ ሳይችሉ፣ተጠያቂነት ሲነሳ አሮጌውን ፍረጃ እየደገሙ ከ60ዎቹ ትውልድ ፖለቲካ ተላቀናል ይሉናል፡፡

ኢ/ሩ አሮጌውን ፍረጃቸውን ለማስረዳት አንድነት፣ቅንጅት፣ኦብኮ፣መኢአድ ላይ የሆነውን በድፍኑ እንደምሳሌ አቅርበዋል፡፡ ሌላው ቀርቶ በሰማያዊና በመኢአድ ላይ የሆነው አንድ አይነት አይደለም፡፡ መቼም ሰርተፍኬቱን ለሰማያዊ ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ ጤና ጥበቃ ይስጥ ካልተባለ በስተቀር፡፡ ሰርተፍኬት ሰጪው አካል አንድ በመሆኑ የሰማያዊ ሁኔታ የሌሎች ተመሳሳይ እንደሆነ የፍረጃው ሞተሮችን ማሳመን ይቻል ይሆናል፡፡ ሂደቱን የተከታተለ ሰው ግን የ’ካፈርኩ አይመልሰኝ ፖለቲካ አስቀያሚ ምሳሌ መሆኑን አይስተውም፡፡ ገና ድርድሩ ሳይጀመር ቅድመ ውይይቱን አስመልክቶ በጥርጣሬ አይን የሚታይ እንደሆነ ስለሚያውቁ ብቻ ያን ለማጠንከር በተለይ የሰማያዊ እና መኢአድ እውቅና ከዛ ጋር እንደሚያያዝ ለማሳየት የሞከሩበት አገላለፅ በፍረጃ ተጠልሎ ለማለፍ የሚሞክሩበትን እርቀት ያሳያል፡፡

የሆነው ሆኖ የኔ ክርክር የግለሰቦች ጉዳይ አይደልም፡፡ ቁም ነገሬ በአመራር ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች በሚፈፅሙት ስህተት የሚፈጠሩትን ችግሮች እስከመቼ በፍረጃና በገዢዎች እያሳበብንና ስህተት የሰሩትን ነፃ እያደረግን እንቀጥላለን? ይህ ለተቃውሞ ጎራው ተዋናዮች የስህተት መደበቂያ ዋሻ ሆኖ አላገለገለም ወይ? እዚህ አገር በተለይ ፓርቲዎች ከመቋቋም ጀምሮ በገዢዎች ተፅእኖ እንደሚደርስባቸው እሙን ነው፡፡ ይህ ከሆነ ለዚህ መሻገሪያውን መንገድ ማዘጋጀት የእነሱ ተግባር አይደለም ወይ? ለዚህ ሀላፊነቱን መወሰድ የለባቸውም ወይ? ይህን ሳንመልስ አለባብሰን አሮጌውን ፖለቲካ መከተል የትም የማያደርስ ብቻም ሳይሆን አንድ እግር ወደፊት አንድ እግር ወደኋላ አይነት ነው፡፡

“በርበሬ አይሆንም ዕጣን ንግግር አይሆንም ሥልጣን” -መነበብ ያለበት የአዲስ አድማስ ርእስ አንቀጽ

$
0
0

አንዳንድ ጨዋታ የዕውነት ያህል አሳማኝ ነው፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን በተባበሩት መንግሥታት ጉባዔ ላይ ከፍተኛ ጭቅጭቅ ይነሳል፡፡ በኃይል ጭቅጭቁን ያካረሩት አራት አገሮች ናቸው፡-
1ኛ/ እንግሊዝ
2ኛ/ ፈረንሣይ
3ኛ/ እሥራኤል
4ኛ/ ሩማኒያ
እንዲያ በኃይል ያጨቃጨቃቸው አጀንዳ፤ “አዳምና ሔዋን የየት አገር ሰዎች ናቸው?” የሚለው ጉዳይ ነው፡፡
በመጀመሪያ ሙግቷን ያቀረበችው እንግሊዝ ናት፡፡ እንዲህ ነው ያለችው፤ በተወካይዋ አማካኝነት፤
“አዳምና ሔዋን ያለጥርጥር እንግሊዞች ናቸው፡፡ ለምን ቢባል፤ እንግሊዛዊ ሰው ብቻ ነው አንዲት ሴት ትፈጠር ዘንድ በጨዋነት የገዛ ጎድኑን አሳልፎ የሚሰጥ”
ይሄኔ የፈረንሳዩ ተወካይ ከመቀመጫው ተፈናጥሮ ተነሳና፤
“በጭራሽ እንደዛ አይሆንም! እስቲ የአዳምን ቁመናና ቁንጅና ተመልከቱ፡፡ ራቁቱን ሆኖ እንኳን እንዴት እንደሚያምር ልብ – በሉ፡፡ ይሄ ሊኖረው የሚችለው ፈረንሳዊ ብቻ ነው” አለ፡፡
ቀጥሎ የቀረበው ተሟጋች እሥራኤላዊው ተወካይ ነበር፡፡ እንዲህ አለ፡-
“በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በትክክል እንደተቀመጠው፤ፍጥረት የተፈጠረው በቅድስቲቱ ምድር ነው፡፡ ስለዚህም አዳምና ሔዋን የተመረጡት ህዝቦች ናቸው! ስለሆነም አይሁዳውያን ናቸው!”
ይሄኔ የሩማኒያው ተወካይ ጭንቅላቱን እየነቀነቀ ብድግ አለና፤
“የለም! በእኛ በሩማንያን ዕምነት አዳምና ሔዋን ሊሆኑ የሚችሉት ሩሲያዊ ነው!”
“እንዴት? አስረዳና?” ብለው ሁሉም ጮሁበት፡፡
የሩማንያው ተወካይም፤
“ምክንያቴን ላቅርብላችሁ፡፡ በዓለም ላይ ሩሲያዊ ብቻ ነው በደንብ ሳይበላና በደምብ ሳይለብስ ገነት ውስጥ ነው ያለሁት የሚል!” ሲል ገለፀ፡፡
ተጨበጨበለት!!
*   *   *
አገርን ከሌላ አገር ማስበለጥ፣ የራስን ፓርቲ ከሌላው ፓርቲ የበላይ ነው ለማለት መሞከርና እኔ እሻል እኔ እሻል መባባል፣ ጥንትም ነበረ፣ አሁንም ያለ እና ወደፊትም የሚኖር ነው፡፡ ያም ሆኖ ያላንዳች ምክናዊነት፣ አንዱ ሌላውን መብለጥ አይችልም፡፡ አመክንዮ ይፈልጋል፡፡
በሀገር ደረጃ ሲታይ ከፖለቲካ ጥንካሬ እስከ ኢኮኖሚ ጥንካሬ፣ ከዚያም የወታደራዊ አቅም፣ እንዲሁም ማህበራዊ መሰረትን ይጠይቃል፡፡ እነዚህን ለማሟላት ብርቱ ድካም፣ የረዥም ጊዜ ባለታሪክ መሆንንም ይጠይቃል፡፡
በሀገራችን ያየናቸው ለውጦች ከወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት፣ እስከ ተማሪ እንቅስቃሴ፣ ውለው አድረውም የተደራጁ ወታደራዊ ኃይሎች አመራር ሥር የወደቁ ነበሩ፡፡ በዚሁ ዙሪያ የተደራጁ ፓርቲዎችና ድርጅቶች ተወልደዋል፡፡ ወደ ትጥቅ ትግልም ያደጉ ታይተዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ግን እርስ በርስ ከመቆራቆስና ከመጠላለፍ፣ አልፎ ተርፎም ከመጨራረስ በስተቀር ሁነኛ የፖለቲካ መድረክ ፈጥረው፣ ሁነኛ ክርክርና ሀቀኛ ሙግት ተሟግተው፣ እዚህ ስምምነት ላይ ደረሱ የሚባልላቸውና የሚያኮሩ አልተገኙም፡፡ መንግሥትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣አይጥና ድመት ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ነበሩ፡፡ ክፍተቱ ሰፊ ነው፡፡ እስከ ዛሬ ስናይ የኖርነው፤ የቂም በቀል፣ የደባና የሤራ፣ ከእኔ በላይ ላሣር እና የደም መፈላለግ ፍጥጫ በመሆኑ የሰላማዊ ትግል ጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ፣በሰለጠነ መልክ ተነጋግሮ ዳር መድረስ ያልተሞከረ ነው፡፡ አንድ ፀሐፊ እንዳለው፤ “የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ ሁሉ በየኪሱ ትናንሽ ዘውድ ይዞ ነው የሚዞረው!”
ከተማሪ እንቅስቃሴ ጊዜ ጀምሮ እንደመሪ መፈክር ሲያገለግል የኖረው፤
‹‹unity is power››
‹‹አንድነት ኃይል ነው›› የሚል ነበር፡፡
“United, we stand
Separated, we fall!›› የሚልም ነበር፡፡ (‹‹ከተባበርን እንቆማለን፤ከተነጣጠልን እንወድቃለን!›› እንደ ማለት ነው፡፡) በአጭሩና በተለመደው የአማርኛ አባባል፤‹‹ድር ቢያብር አንበሳ ያሥር›› ማለት ነው፡፡ ይሄ ዛሬም ይሠራል፤በአግባቡ የሚጠቀምበት ከተገኘ፡፡ ጥበብ ይጠይቃል፡፡ በሆይ ሆይታና በግርግር፤ በችኮላ የሚፈጠር አካሄድ መጨረሻው አያምርም፡፡ የፖለቲካ ድርድር የአንድ ወገን ብልጠት አይደለም፡፡ የሀገር ጉዳይ ነውና ሁሉም ወገን በልባዊነት ሽንጡን ጠበቅ ሊያደርግበት የሚገባ ነገር ነው፡፡ በተንኮል ሽረባም የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን፤
‹‹ነገር በሆድ ማመቅ
ለትውልድ መርዝ መጥመቅ›› የሚለን ለዚህ ነው!
ከሁሉም በላይ መቻቻል የሚፈተንበት፣ሆደ-ሰፊውና አስተዋዩ የሚለይበት ነው። የፖለቲካ ብልህነት ጠርቶ የሚወጣበት ነው፡፡ ዲሞክራሲ የተሸናፊዎች መብት መሆኑን በእርግጥ የምናጣራበት ሂደትም ነው፡፡ ገዢው ዘራፍ ሳይል፣ተገዢው በቂምና በቅሬታ ሳይወጣ ማየት እንሻለን፡፡ ሰላማዊ ትግል የሰላም አገር መለያ ነውና፣ከትንቅንቁ ባሻገር ግልፅ ውይይት እንጠብቃለን፡፡ ስለታሰሩ የተቃዋሚ አባላት ምን ሀሳብ እንደሚነሳ ለመስማት እንጓጓለን፡፡ ስለምርጫ ህግጋት ለውጥ ምን እንደሚወሳ ለማዳመጥ እንተጋለን፡፡ በመጨረሻ ግን አንደበተ ርቱዕነት ብቻውን የአሸናፊነት መገለጫ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ ቀናነት፣ ቁጡነትን ማስወገድ፣ የቤት ሥራን በሚገባ ሰርቶ መምጣት፣ ወቅታዊ (timely) የሆነውን ጉዳይ፤ ጊዜ ከማይሽረው (timeless) ጉዳይ ለይቶ ማየት ወሳኝነት አላቸው፡፡ ከሁሉም በላይ ግን፤
‹‹በርበሬ አይሆንም ዕጣን
ንግግር አይሆንም ሥልጣን››
የሚለውን አባባል አለመዘንጋት ነው! ይሄን ልብ እንዲሉም አደራ ጭምር እናስታውሳለን፡፡

በጎንደር ችግር አለ – ብአዴን ህዝብን ሲያናግር፣ ሕወሃት ይተኩሳል – የሚሊዮኖች ድምጽ

$
0
0
 
ጎንደር ከተማ ከፍተኛ ተኩስ እንዳለ እየተገለጸ ነው። ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋው “ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ፣ ከምሽተ 4.30 ጀምሮ መኖሩን መረጃዎች እየመጡ ነው። ከፍተኛ የሆነ ውጥረት ሲኖር መንገዶች ሁሉ ተዘግተዋል ተብሏል” ሲል ጦምሯል።
 
ከጥቂት ቀናት በፊት የብአዴን ከፍተኛ አመራር አባላት የከተማዋን ህዝብ በአክብሮት ማነጋገራቸውና ሕዝቡ አስተያየቱን በድፍረትና በወኔ መስጠቱን በተመለከተ በሰፊው መዘገቡ ይታወቃል። ሆኖም ግን፣ የብአዴን አመራሮች ሕዝቡን ለመስማት ባደረጉት ጥረት ያልተደሰቱት፣ ኮምንድ ፖስት ከሚባለው ጀርባ ያሉ የሕወሃት የደህነትና የመከላከያ ሃላፊዎች ” እነ ገዱ የፈለጉትን ስብሰባ ጠርተው ቢያወሩም ከኛ ዉጭ የትም አትሄዱም። ሃይሉ ያለው እኛ ጋር ነው” በሚል የደካሞችና የእብሪተኖችን መለስክት ለማስተላለፍ ፣ ሆን ብለው የጀመሩት ጠብ ጫሪነት ሊሆን እንደሚችል ተንታኞች ይናገራሉ።
 
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ታዉጆ፣ በርካታ ታጣቂዎች በመላክ አገዛዙ መረጋጋትን ለመፍጠር የሞከረ ቢሆንም፣ እንደ ጎንደር ከተማና ባህር ዳር፣ ካሉ ትላልቅ ከተሞች ዉጭ፣ በሌሎች ገጠራማ አካባቢዎች ከአገዛዙ ቁጥጥር ዉጭ እንደሆኑና በጎበዝ አለቃ የሚመሩ፣ ከሕዝቡ የተወጣጡ በርካታ ተዋጊዎች፣ የሚንቀሳቀሱባቸው እንደሆነ ለአካባቢው ቅርበት ያላቸው ይናገራሉ። አገዛዙ አካባቢውን ማረጋጋት ባለመቻሉም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በአማራው ክልል እንደገና ለሶስት ወራት ለማስተላለፍ እቅድ እንዳለውም ታውቄል።
 
መሳሪያ፣ ሃይል ፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መፍትሄ እንዳላመጣና እንደማያመጣ የገለጹትአንድ የቀድሞ ዝነኛው የአንድነት ፓርቲ ክፍተኛ አመራር አባል ” ያ ሁሉ ወታደር ተሰማርቶ፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታዉጆም፣ መረጋጋት ካልመጣ፣ ኢሕአዴግ ከሃይልና ከእልህ ፖለቲክ ያለፈ ተሻለ አማራጫን መቀበል አለበት ” ሲሉ አገዛዙ መሰረታዊ የአካሄድ ለዉጥ ካላመጣ የከፋ ችግር ዉስጥ እንደሚወድቅ ነው የተናገሩት። እኝህ የሰላማዊ ታጋይ ሲያክሉም አሁን ተጀመረ የተባለውን ድርድርን፣ ኢሕአዴግ ለሰላም፣ ለአገር ጥቅም ብቻ ሳይሆን ለራሱ ሲል እንዲጠቀምበት፣ በሕዝብ ተቀባይነት ያለው፣ የተጨበጠ ዉጤት የሚያመጣ ድርድር እንዲያደርገው ጠይቀዋል።
 
“ፍርሃት የወለደው ታጋሽነታችን ለብዙ ሕገ-ወጥ ድርጊት ጋብዞናል” የሚለው መፈክር በጎንደር ሲታይ የነበረ መፈክር ነበር። ” መንግስት ለኔ ሳይሆን በኔ ላይ ነው የቆመው” የሚል እምንት በዉስጡ ካዘለ፣ አገዛዙ የሚያወጣውን ሕግ በሙሉ አልቀበለም የሚል የእምቢተኝኘት አቋም መያዙ አይቀረም። ተጀምሯልም።
 
በመሆኑም አገዛዙ እንደከዚህ በፊቱ ሊቀጠል እንደማይችል ተገንዝቦ፣ የይስሙላን እና የማስመሰንልል የዉሸት “ተሃድሶዉን” ወደ ጎን ጥሎ፣ አንድ የጎንደር ነዋሪ እንዳሉት በድሪቶ ላይ ድሪቶ መደረቡን አቁሞ፣ ለትክክለኛና እዉነተኛ፡ለዉጥ ራሱን እንዲያዘጋጅ እንጠይቃለን።
 
ከተቃዋሚዎች ጋር የተጀመረዉ ድርድር እንደ አገር ከታሰርነበት ማነቋችን የምንወጣበት፣ የሰደዱ የሚመለሱትብት፣ ነፍጥ ያነሱ ነፍጥ የሚደፉበት፣ የታሰሩ የሚፈቱበት፣ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተበተኑ የሚሰባሰቡበት፣ በዘር አድሎ ሳይኖር ሁሉም እንደ ኢትዮጵያዊ በዜግነቱ የሚከበርባትና ሁሉ በሁሉም የአገሪቷ ግዛቶች በሰላም የሚኖሩባት ኢትዮጵያ ትመጣ ዘንድ በሩን የሚከፍት ድርድር እንዲሆን ጸሎታችን ነው።

Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”

ዶ/ር መረራ የኦሮሚያን ብጥብጥ በማባባስና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመጣስ ክስ ተመሠረተባቸው – ታምሩ ጽጌ

$
0
0
  • በክሱ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ ጀዋር መሐመድ ተካተዋል

የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ ባደረገላቸው ጥሪ ቤልጂየም ብራሰልስ ደርሰው ሲመለሱ፣  ከመስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሆነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በመጣስ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረውን ብጥብጥና ሁከት ሲያባብሱ እንደነበር የሚገልጽ ክስ ሐሙስ የካቲት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ተመሠረተባቸው፡፡

የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1ሀናለ)፣ 38(1)ን፣ 27(1)ን እና አንቀጽ 238 (1 እና 2)ን ተላልፈዋል ተብለው የመጀመሪያ ክስ የተመሠረተባቸው ዶ/ር መረራ፣ የግንቦት ሰባት አርበኞች ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ ጀዋር መሐመድ ናቸው፡፡ በፌዴራልና በክልል ሕገ መንግሥት የተቋቋመን ሥርዓት በሕገወጥ መንገድ ለማፍረስ መንቀሳቀሳቸውን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የመሠረተው ክስ ያስረዳል፡፡ የፖለቲካ፣ የሃይማኖት ወይም የአይዲዮሎጂ ዓላማን ለማራመድ፣ በመንግሥት ላይ ጫና ለመፍጠርና ኅብረተሰቡን ለማስፈራራት፣ ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ የሁከትና የብጥብጥ ጥሪ በማስተላለፍ በአንዳንድ የአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ኅብረተሰቡ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እንዲገባ ማድረጋቸውን፣ ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ባቀረበው ክስ ገልጿል፡፡

ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንዳብራራው ዶ/ር መረራ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራርነትን እንደ ሽፋን ተጠቅመው፣ የአዲስ አበባ ከተማና የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላን ተቃውሞን እንደ መነሻ በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እንዲቀጥል አድርገዋል፡፡

በ2006 ዓ.ም. ለኦፌኮ አባላት የሥራ ክፍፍል በማድረግ በመንግሥትና በሕዝብ ተቋማት፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ላይ የንብረት ውድመት እንዲደርስ ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ በኢንቨስትመንት ላይ በተሰማሩ ባለሀብቶች ንብረቶች ላይም ውድመት መድረሱንም አክሏል፡፡ በሰውም ላይ ከባድ የአካል መጉደልና ሞት መከሰቱንም ጠቁሟል፡፡

ዶ/ር መረራ በ2008 ዓ.ም. በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች በተለይም በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ አካባቢ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ማለትም የአምቦ-ካራ የመንገድ ግንባታን በመቆራረጥ፣ ካምፕ በማቃጠል፣ በተሽከርካሪዎችና በማሽነሪዎች ላይ የ2,957,661 ብር ንብረት እንዲወድም ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ በቡራዩ ከተማም በ42,598,204 ብር ንብረቶች ላይ ጉዳትና ውድመት ማድረሳቸውንም አክሏል፡፡ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ፣ አመያ፣ ጎሮ፣ ቶሌ፣ ኢሉ፣ ቀርሳ፣ ወንጪ ወረዳዎችና ቀበሌ መስተዳድር የግለሰቦች መኖሪያ ቤቶችንና በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ኢንቨስተሮችን የተለያዩ ንብረቶች ጉዳት በማድረስና በማውደም የ17,352,482 ብር ጉዳት እንዲደርስ ምክንያት መሆናቸውንም ክሱ ያብራራል፡፡

ሐምሌ 28 ቀን 2008 ዓ.ም. በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ዶ/ር መረራ ባስተላለፉት የሁከት ጥሪ፣ ሐምሌ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. በመላ ኦሮሚያ ሕዝባዊ ተቃውሞ ለማካሄድ መታሰቡን በመግለጽና የሁከቱ ተካፋዮች እንዲሳተፉ ጥሪ ማቅረባቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

ዶ/ር መረራ ለዚሁ መገናኛ ብዙኃን መስከረም 24 ቀን 2009 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ኢሬቻ በዓል ላይ የተከሰተውን አደጋ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ የመንግሥት ታጣቂዎች በኦሮሚያ ሕዝብ ላይ በወሰዱት ግድያ 678 ሰዎችን እንደተገደሉ በመግለጽ ባስተላለፉት ጥሪ፣ በክልሉ አንዳንድ ከተሞች ሁከትና ብጥብጡ እንዲቀጥል ማድረጋቸውን ክሱ ያብራራል፡፡ በተነሳውም ብጥብጥና ሁከት የሰላማዊ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን፣ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ በመንግሥትና መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ፣ እንዲሁም በኢንቨስትመንት ላይ በተሰማሩ ባለሀብቶች ንብረቶች ላይ ጥቃት እንዲደርስና እንዲወድሙ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በኢሉአባቦራ፣ በምዕራብ ሸዋ፣ በምሥራቅ ሸዋ፣ በባሌ፣ በሰበታ ከተማ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ በአርሲ፣ በምዕራብ አርሲ ዞን በመንግሥት ንብረት ላይ የ215,468,309 ብር ውድመት እንዲደርስ ማድረጋቸውንም ገልጿል፡፡ ዶ/ር መረራ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ንብረት ላይ የ1,168,293,498 ብር ንብረት እንዲወድም ምክንያት መሆናቸውንም በክሱ አብራርቷል፡፡

ሌላው ዶ/ር መረራ በቁጥጥር ሥር ውለው የታሰሩበት ምክንያት መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በመጣስ ተብለው ነው፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ከተፈረጀው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር በብራሰልስ በመገናኘታቸው ዓቃቤ ሕግ ክስ መሥርቶባቸዋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ አዋጁን ለማስፈጸም በወጣው መመርያ በሽብርተኝነት ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር መገናኘት የተከለከለ መሆኑ ተገልጾ እያለ፣ ዶ/ር መረራ መመርያውን ጥሰው በመገናኘታቸውና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 01/2009 አንቀጽ 12(1)ን በመተላለፋቸው መሆኑን ክሱ ያብራራል፡፡

ዶ/ር መረራ ኅዳር 2 ቀን 2009 ዓ.ም. ከፕሮፌሰር ብርሃኑ ጋር በብራሰልስ የኦኤምኤን ሠራተኞችና የኦነግ አባላትና ደጋፊዎች ባዘጋጁት የስብሰባ መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ስለነበረው ሁከትና ብጥብጥ በመግለጻቸው፣ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር የተያያዙ ግዴታዎችን የመተላለፍ ወንጀል በመፈጸም ክስ ዓቃቤ ሕግ አቅርቦባቸዋል፡፡

ዶ/ር መረራ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 486(ለ)ን በመተላለፍ በ2006 ዓ.ም የኢትዮጵያና ናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድኖች በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚያደርጉት ጨዋታ የአልሸባብ አባላት የአጥፍቶ ማጥፋት ወንጀል ለመፈጸም ባለመቻላቸውና የታጠቁት ፈንጂ ፈንድቶ መሞታቸው እየታወቀ፣ እሳቸው ግን ‹‹አሸባሪዎቹ አፈነዱ የተባለው የውሸትና የመንግሥት ድራማ ነው›› በማለት ሕዝቡ በመንግሥት ላይ እምነት እንዳይኖረው አድርገዋል ሲል ዓቃቤ ሕግ የሐሰት ወሬዎችን የማውራት ወንጀል ክስ መሥርቶባቸዋል፡፡

ከዶ/ር መረራ ጋር በአንደኛ ክስ ተካተው ክስ የተመሠረተባቸው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ ጀዋር መሐመድ ናቸው፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በህቡዕ አባላትን በመመልመል እንዲንቀሳቀሱ በማድረግ፣ ሁከቱ እንዲቀጥል በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) በተለይ በ2009 ዓ.ም. የሁከት ጥሪ ማድረጋቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ አርሶ አደር ከእንግዲህ ግብርና የማዳበሪያ ዕዳ አይከፍልም፤›› በማለት አርሶ አደሩ በመንግሥት ላይ እንዲያምፅና ለፍትሕ ሥርዓቱ እንዳይገዛ የሁከት ጥሪ ማቅረባቸውንም አክሏል፡፡ እሳቸውም ሆኑ ድርጅቱ አርበኞች ግንቦት ሰባት እስከ መጨረሻው የደም ጠብታ ድረስ እንደሚታገሉ በመግለጽና በሰላማዊ መንገድ መታገል ሞኝነት መሆኑን በመስበክ፣ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የሚገኘው ሕዝብ መሣሪያውን እየወለወለ ወደ በረሃ እንዲገባም በኢሳት ቴሌቪዥን ንግግር በማድረግ፣ ሁከቱና ረብሻው በመላ አገሪቱ እንዲስፋፋ ጥሪ ማቅረባቸውንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡ ፕሮፌሰሩ በተለያዩ ጊዜያት በአገር ውስጥ በህቡዕ የሚንቀሳቀሱ ባሉበት ጥቃት እንዲያደርሱ በመንገር፣ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የሽብር ቡድን አባላትም ተመሳሳይ ተግባር እንዲፈጽሙ ትዕዛዝ መስጠታቸውንም ክሱ ያብራራል፡፡

አቶ ጀዋር መሐመድም የአዲስ አበባ ከተማና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላንን ለሁከት መቀስቀሻ ምክንያት በማድረግ፣ በአገር ውስጥ ለሚገኙ የኦነግ የሽብር ቡድን አባላት ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ በኦሮሚያ ክልል የነበረውን ብጥብጥና ሁከት በኦኤምኤን በማስተላለፍ ሁከትና ብጥብጡ እንዲቀጥል ጥሪ ሲያደርጉ እንደነበር በክሱ ተጠቅሷል፡፡ ከወቅቱ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ነጋዴዎች ለሕዝቡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን እንዳይሸጡ፣ እንዳያቀርቡና እንዳይገዙ፣ የትራንስፖርት አቅርቦት እንዳይኖር በማለት የሁከት ጥሪ መግለጫዎችን ሲያስተላልፉ እንደነበር በክሱ ተብራርቷል፡፡ አቶ ጀዋር ከላይ በዶ/ር መረራ ክስ ላይ የተገለጹ የንብረት ውድመቶች (በገንዘብ የተገለጹት) እንዲደርሱ ምክንያት መሆናቸውንም ክሱ ይጠቁማል፡፡

በመሆኑም ሦስቱም ተከሳሾች በፈጸሙት በሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማስወገድ ሙከራ ወንጀል መከሰሳቸውን፣ የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ ዓቃቤ ሕግ የጠቀሰውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 238 (1 እና 2)ን ተላልፈው ፈጽመውታል የተባለው ወንጀል በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች ከተረጋገጠ፣ ከሦስት ዓመታት እስከ ሞት ሊያስቀጣቸው እንደሚችል ሕጉ ይገልጻል፡፡

በክሱ ውስጥ በሁለተኛ ክስ ላይ የተካተቱት ድርጅቶች ደግሞ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና ኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (ኦኤምኤን) ናቸው፡፡ ድርጅቶቹ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1)ሀ እና ለ፣ 38፣ 34 (1)እና የሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5 (1) ለን በመተላለፍ፣ ዶ/ር መረራ፣ ፕሮፌሰር ብርሃኑና አቶ ጀዋር ደግሞ ‹‹ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በሁከትና ብጥብጥ እናስወግዳለን፤›› በማለት ያቀረቡትን ጥሪ በማስተላለፍ ድጋፍ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አብራርቷል፡፡ መገናኛ ብዙኃኑ በተለያዩ ጊዜያት ያስተላለፉትን ጥሪ ዓቃቤ ሕግ በዝርዝር በክሱ አካቶ አብራርቷል፡፡ በአጠቃላይ ድርጅቶቹ የኦነግና የአርበኞች ግንቦት ሰባት ልሳን በመሆንና ሚዲያንና ሙያን ሽፋን በማድረግ፣ ሦስቱ ግለሰቦች የሚያስተላልፉትን የብጥብጥ ጥሪ በመቀበልና የሽብር ቡድን ድጋፍ በማድረግ በዋና ወንጀል ላይ ተካፋይ በመሆናቸው፣ የሽብር ተግባር ወንጀል ክስ እንደተመሠረተባቸው ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡

ክሱ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ለዶ/ር መረራ ጉዲና ክሱን በመስጠት ለማንበብና ተከሳሹ በጠበቃ ተወክለው እንዲቀርቡ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከስድስት ዓመታት በፊት ክስ ተመሥርቶባቸው በሌሉበት በሞት እንዲቀጡ ፍርድ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”


Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”

የአለቃ ጸጋየ በርሄና የህላዊ ዮሴፍ ወጎች፤ ከሹመት እስከ ሽረት፤

$
0
0
  • የህወሓት-እስራኤል ቀጣይ የፖለቲካ ቁማር!

አሁን ባለዉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፍ ለህወሓት/ኢህአዴግ ቁልፍ የስጋት ምንጩ የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ጎራ ነዉ፡፡ የድህረ-ምርጫ 97 ዉርስ ዕዳ የሆነዉ የዲያስፖራዉ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እንደ ሀገር ቤቱ ሁሉ በዘዉግ ፖለቲካ የሚታመስ ቢሆንም በጋራ ጠላት (ህወሓት/ኢህአዴግ) መዉደቅ ላይ ያለ አንዳች የልዩነት መስመር ይስማማል፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ ሀገር ቤት ያሉት የተቃዉሞ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ከሚያሰሙት ጩኅት በላይ ከባህር ማዶ የሚሰማዉ ሹክሹክታ እንቅልፍ ይነሳዋል፡፡ የህዝብ ድምጽና የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ፖለቲካ መሳ ለመሳ መሄድ የቆላ ቁስል ሆኖበታል፡፡ እናም የዲፕሎማሲ ታርጋን እንደ ሴራ ፖለቲካና ድርጅታዊ ጠቀሜታነት አብዝቶ ለመጠቀም የጨዋታዉን ህግ ያሻሻለ ይመስላል፡፡

የዲያስፖራ ፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪነት በማይካድ ደረጃ አይሎ በመዉጣቱ ወትሮዉንም ጥንቃቄ ይደረግበት የነበረዉ የአምባሳደሮች ሹመት ቁልፍ ቁልፍ በሆኑ ሀገራት የህወኃት ሰዎች አለያም ለድርጅቱ ቀይ ምንጣፍ ሊጎትቱ ለሚችሉ የኢህአዲግ አባል ድርጅቶች ዉስጥ አባላት መሆን እንዳለባቸዉ የህወሓት ነባር ታጋዮች የማይሻር ህግ ነዉ፡፡

አሁን ባለዉ ተጨባጭ ሁኔታ ብረት አከል ሁለገብ ትግል (ገጠር-ከተማ የሚያዳርስ የተጠና የትግል ስልት) በሚሹ ኃይሎችና በወታደራዊ ዕምቃ ሥልጣናቸዉን ሊያጸኑ በወሰኑ መንግስታዊ ሽፍቶች መሀከል የሚዋልል ፍትጊያ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መገለጫ ሆኗል፡፡

የሰላማዊ ትግል ጀምበር ባዘቀዘቀባት ኢትዮጵያ፤ ከወራት በፊት ተራዛሚነት ባሳየ መልኩ ለተቀጣጠሉት ህዝባዊ አመጾች የሞራልና የሎጀስቲክ ድጋፎችን በተናጠልና በግብረ-ኃይል ደረጃ በማድረግ የዲያስፖራዉ ሚና ላቅ ያለ ነዉ፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ላለፉት ሃያ አምስት አመታት ያለ መታከት እንቅልፍ አጥቶ ይሰራበት የነበረዉ ጸረ-ኢትዮጵያ አጀንዳ በድካሙ ልክ አልሆንለት ብሏል፡፡ ይህን አዉዳሚ ጸረ-ኢትዮጵያ አጀንዳዉን በማክሸፍ ረገድ የዲያስፖራዉ ሚና ከነችግሩም ቢሆን በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ በተለይም በሀገር ቤት የሚታየዉን የሰብዓዊና የዴሞክራሲ መብቶችን ረገጣ ለምዕራቡ ዓለም በማስተጋባት፤ ዘዉግን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን በማስረጃ አስደግፎ በማጋለጥ፤ “ትግራይ እስክትለማ ኢትዮጵያ ትድማ!” የሚለዉን ህወሓታዊ “የዘዉግ ኢኮኖሚክስ” ገመና አደባባይ ላይ በማስጣትና መሰል ጉዳዮችን በማንሳት የዲያስፖራዉ የተቃዉሞ ጎራ ተጽዕኖ ከቃላት በላይ ነዉ፡፡

ላለፉት ሃያ አምስት አመታት ስንሰማዉ ከኖርነዉ እዉነታ አኳያ በዉጭ ሀገራት በአምባሳደርነት የሚሾሙን፣ የደህንነትና የፖለቲካ አታሼዎችን እና የኢምባሲ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ምደባ በጌታቸዉ አሰፋ የሚመራዉ የደህንነት ቢሮዉና ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ የሚሰሩት መሆኑን ነዉ፡፡ ህወሓት ከአናሳ ዘዉግ የተገኘ የፖለቲካ ቡድን እንደመሆኑ መጠን የሰዉ ኃይል ዉስንነት አለበት፡፡ ህወሓት የራሱን ሰዎች በሁሉም ቦታ ለመመደብ ዲፕሎማሲያዊ አካሄዶችና የሰዉ ኃይል ዉስንነት ቢያግደዉም በዋናዋና ሀገራት ከፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አኳያ የራሱን ሰዎች ቢቻል በአምባሳደርነት ቦታ ካልሆነም በኢምባሲ ዋና ጸሃፊነት፤ የፖለቲካና የደህንነት አታሼ ቦታዎች ላይ ማስቀመጥ ለድርድር የማያቀርበዉ አቋሙ ነዉ፡፡

እንዲህ ያለዉን ተሞክሮዉን ይበልጥ ለመረዳት በሰሜን አሜሪካ፣ ካናዳ፣ አዉስትራሊያ፣ በአዉሮፓ ዋና ዋና ሀገራት (እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ኖርዌ፣ ቱርክ) በኤዥያ (ህንድ፣ ጃፓን፣ቻይና፣ ደቡብ ኮርያ፣ ሲንጋፖር) በመካከለኛዉ ምስራቅ (የተባበሩት አረብ ኢሜሬት፣ ኳታር፣ሳዉዲአረቢያ፣ ኩዌት፣ እስራኤል) በአፍሪካ (ሁለቱም ሱዳኖች፣ ኬንያ፣ ግብጽ፣ ደቡብ አፍሪካ) ባሉ ሀገራት የአምባሳደር ሹመቶችንና በታኮነት የተቀመጡትን ወሳኝ የኢምባሲዉን ሰራተኞች ማንነትና ፖለቲካዊ ስብዕና ማጤኑ ይበልጥ ግንዛቤ ይሰጣል፡፡ ተሹዋሚ አምባሳደሮቹ አንድም የህወሓት ሰዎች ናቸዉ ካልሆነም የድርጅቱ ቀይ ምንጣፍ ጎታቾች መሆናቸዉ ለክርክር የሚቀርብ ጉዳይ አይሆንም፡፡ እዚህ ላይ በአሜሪካና በእንግሊዝ ያሉትን የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሰራተኞችን ለማሳያነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ኃይለ ሚካኤል አበራ

ግርማ ብሩን በአምባሳደርነት ሹመዉ ከጽዳት እስከ ኢምባሲዉ ዋና ጸሃፊ ድረስ፣ ከሴፍቲ ማን እስከ ፖለቲካና ደህንነት አታሼዎች ድረስ ከቪዛ ጉዳዮችን ከሚመለከቱ ሰራተኞች እስከ የዲያስፖራ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊነት ቦታዎች በሙሉ የትግራይ ሰዎች ናቸዉ፡፡ፕሮፖጋዲስቶቹ የህወሓት ሰዎች በየቢሯቸዉ የ“ብሄር ብሄረሰቦች”ን ፎቶ ለጥፈዋል፡፡ የክልሎችን ባንዴራ በየቢሮዉ ተፈልጎ አይታጣም፡፡ በስጋ ህወሓት በመንፈስ ደግሞ “ብሄር ብሄረሰቦች” ዉክልና አላቸዉ፡፡ ለንደን ላይ ብርሀነ ሀጎስን የተካዉ የኤፈርትን ንግድ የሚያጧጥፈዉ ኃይለ ሚካኤል አበራ ኢምባሲዉን ከእግር እስከ ራሱ በትግራይ ሰዎች ሞልቶታል፡፡ ይሄዉ ከሰሞኑ በዉጭ አገራት ባሉ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች የህወሓት 42ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በከበሮ ድለቃ እየተከበረ እንደሆን በመገናኛ ብዙሃን የዜና ሽፋን ተሰጥቶት እያየን ነዉ፡፡ የብአዴንና የኦህዴድን የምስረታ በዓል ማን ዘወር ብሎ ያያል?

ከላይ ለማሳያነት በተጠቀሱት ሀገራት የሚመደቡት አምባሳደሮች ካልተጻፈዉ ቀዳሚ ሥራቸዉ አንዱ ለህወሓቱ ግዙፍ ድርጅት ኤፈርት የሚሆኑ የንግድ ልዉዉጥ ጉዳዮችን ማመቻቸት ሲሆን፤ በግልጽ ከተጻፈዉ ቀዳሚ ሥራቸዉ አንዱ ደግሞ እንደየሀገራቱ ተጨባጭ ሁኔታ ዲያስፖራዉን ቢቻል በአብዮታዊ ዴሞክራሲዉ “የዲያስፖራ ፖሊሲ” እንዲጠመቅ በማድረግ የድርጅቱን ማህበራዊ መሰረት ማስፋት ካልሆነም በዲያስፖራዉ መካከል የዘዉግ ክፍፍል በመፍጠር ኃይሉን ማዳከም አምባሳደሮቹ፣ የፖለቲካና የደህንነት አታሼዎቹ የሥራ አፈጻጸም ከሚገመገምባቸዉ ነጥቦች በቀዳሚነት ይጠቀሳል (እንደየ ሀገራቱ የዲያስፖራ የኃይል ሚዛን ቢለያይም)፡፡

የህላዊ ህልውና ማክተም

የመለስ ዜናዊን ህልፈት ተከትሎ የተፈጠረዉን የዲፕሎማሲ ክፍተት ለመድፈን በየዓመቱ መጨረሻ ወር ላይ በህወሓቱ ኢሳያስ አማካኝነት የዉጭ ገዳዮችን በሚከታተለዉ የደህንነት ቢሮዉ ዲፓርትመንት ሪፖርት አቅራቢነት በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አስተባባሪነት መካሄድ የጀመረዉ የአምባሳደሮች ዓመታዊ ስብሰባ ቀዳሚ አጀንዳ “የጽንፈኞችን ኃይል ለማምከን የተደረጉ ጥረቶችን እና ልማታዊ ዲያስፖራ ለመፍጠር የተሰሩ ተግባራት” የተመለከቱ ጉዳዮችን በስፋት ይቃኛሉ፡፡ ቀናት በሚወስደዉ በዚሁ ስብሰባ የየኢምባሲዉ አምባሳደሮች በመዋቅር ደረጃ ከነርሱ በታች የፖለቲካና የደህንነት አታሼ ሆነዉ በተመደቡ የህወሓት ሰዎች ከፍና ዝቅ እየተደረጉ ይገመገማሉ፡፡ እንዲህ ያለዉ ግምገማ በብርቱ ከደረሰባቸዉ አምባሳደሮች ቀዳሚዉ ህላዊ ዮሴፍ ይገኝበታል፡፡

ህላዊ ዮሴፍ

ህላዊ ዮሴፍ በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ አምባሳደር ሆኖ ከተሾመ አንስቶ ሁለት ዋና ዋና ተልዕኮዎችን ማሳካት ይጠበቅበት ነበር፡፡ የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት የሚያደርጉበትን ሁኔታ ማመቻት በተለይም ከኤፈርት ጋር (የብአዴኑን “ጥረት” እንርሳዉ) የሚሰሩበትን ዕድል መፍጠር አንደኛዉ ተልእኮዉ ነበር፡፡ ሁለተኛዉ ተልዕኮ ደግሞ በእስራኤል የሚኖሩ ትዉልደ ኢትዮጵያዊያንን (ቤተ እስራኤላዊያንን) የዲያስፖራ ፖሊሲ በማጥመቅ መዋዕለ ንዋያቸዉን በኢትዮጵያ እንዲያፈሱ ማግባባት ጎን ለጎን ከቅርብ አመታት ወዲህ በቤተእስራኤላዊያን ዘንድ እየተስተዋለ ያለዉን የአንድት ሃይሉን በገንዘብ የመደገፍ ስሜት ማስተንፈስ የህላዌ ዮሴፍ ቁልፍ ተልእኮዎች ነበሩ፡፡ በእርግጥ በእስራኤል የኢትዮጵያ ኢምባሲ ዉስጥ ሶስተኛ ተልእኮም አለ፡፡ እስራኤል እንደ መንግስት ህወሃት እንደ ድርጅት በደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ከሞሳድ ጋር የሚሰሯቸዉ ተግባራት አሉ፡፡

እስራኤልና አሜሪካን ሶማሊያ ዉስጥ ከመሸገዉ የአልሸባብ የሽብር ጥቃት ለመጠበቅ በዉክልና የሚዋጋዉ ህወሃት ለዚህ ዉለታዉ ከቴክኖሎጂ አቅም ጋር በተያያዘ የደህንነትና ስለላ (በተለይም ከሽብተኝነት ጋር በተያያዘ) እንዲሁም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነትና ስለላ የተመለከቱ ስልጠናዎች ለህወሃት ምልምሎች ይሰጣል፡፡ የስልጠና ተሳታፊዎችን የስልጠና ሂደቱን የሚከታተለዉ በኢምባሲዉ በኩል የደህንነት አታሼ ቡድን አለ፡፡ ህላዌ ይህን ጉዳይ ዳር ቁሞ ከመታዘብ የዘለለ ሚና አልነበራዉም፡፡

ያም ሆኖ “የእስራኤል ባለሃብቶችን ወደ ኢትዮጵያ በሚገባ አልሳብክም፤ ለኤፈርት ይህ ነዉ የሚባል የገበያ ትስስር አልፈጠርክም፤ በቤተእስራኤላዊያን ዲያስፖራዎች መዋዕለ ንዋያቸዉን በኢትዮጵያ እንዲያፈሱ ማግባባት አልቻልክም፤ በተለይም በ2008ዓም ሃምሌ ወር ላይ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ በባህር-ዳር ከተማ በተከበረዉ የዲያስፖራ ቀን ከእስራኤል የመጡት ዲያስፖራዎች ሰባት ብቻ ነበሩ፡፡ በአንጻሩ ቴልአቪቭና ጎንደር ከተማን ለመለየት በሚያስቸግር መልኩ ቴልአቪቭ የትምክህተኞችና የፀረ- ሰላም ሃይሎች ማዕከል ስትሆን አንተ ቢሮህን ዘግተህ ልቦለድ ታነብ ነበር” በሚሉ ቅስም ሰባሪ ክሶች በመዋቅር ደረጃ የበታቾቹ በገቢር ግን አለቆቹ በሆኑት የኢምባሲዉ የፖለቲካና የደህንነት አታሼዎች ተገምግሞ በእነ ጌታቸዉ አሰፋ ይሁንታ ሰጪነት በኃይለማርያም ደሳለኝ ፈራሚነት ከአምባሰደርነቱ ተነስቷል፡፡ በምትኩም የምንግዜም የበላዩ የህወሃቱ አለቃ ፀጋዬ በርሄ ተሹሟል፡፡

“የህላዌ አዕምሮ ኢህአፓ ላይ ቁሟል፡፡ ከዚህ በኋላ አዕምሮዉን ለግጥም እንጂ ለፖለቲካ ሊያዉለዉ አልቻለም” የሚሉት የኢህዴን የቀድሞ ታጋዮች፤ የመጠሪያ ስሙን ከፍቅሩ ዮሴፍ ወደ ህላዊ ዮሴፍ ከቀየረ በኋላ ከርዕዮተ ዓለማዊ ምልከታ ይልቅ የግጥም ተመስጦዉ በረታ፡፡ በድህረ ደርግ የመጀመሪያዉ አዲስ ዓመት ማግስት የህላዊ ብቸኛ ወንድም በአዲስ አበባ አንድ ጥግ ቦታ ላይ ራሱን አጥፍቶ ተገኘ፡፡ ህላዊ ከዚያች ቀን ጀምሮ ግድየለሽና ዝርክርክ ሰዉ ሆነ፡፡ አልኮልን ዋኘበት፡፡ ሲጋራን ከብዕሩ በላይ ጨበጠ፡፡ በበረከት ስምኦንና በጥቂት ጓዶቹ ጥረት ህይወትን በሹፈት፤ ፖለቲካን በአስመሳይነት ቀጠለ፡፡

ለዚህም ይመስላል የርጅና ዘመኑ አስቀድሞ የመጣ፡፡ በአምባሳደርነት ግዜዉ የኢየሩሌምን ገዳማት አዘዉትሮ ይጎበኝ ነበር፡፡ ቴልአቪቭ ዉስጥ በሚገኘዉ አዲስ አበባ ሬስቶራንት በተደጋጋሚ  ከሚገኙ ደንበኞች ቀዳሚዉ እርሱ ነዉ፡፡ በህወሃት ሰዎች አጠራር “በአዝማሪ ድግስ/ኮንሰርት” መታደም ነፍሱ ነዉ፡፡ ጠርሙስ ባይወረወርበትም አሽሙር ተወርዉሮበት ወደ ቤቱ ይመለስ ነበር፡፡ ቢሮዉ ዉስጥ በአዳም ረታ የልቦለድ ስራዎች መዝናናት ይወድ የነበረዉ ህላዌ፤ “የስንብት ቀለማት” እና “መረቅ” የተሰኙ የደራሲዉ ስራዎች ቢሮዉ ጠረጴዛ ላይ አይጠፉም፡፡

በእነዚህና መሰል ድርጊቶቹ ለተከታታይ ሁለት አመታት “C” በስንብት ዘመኑ ደግሞ “D” የተሰኘ አሸማቃቂ የአምባሳደርነት ዉጤቱን ተቀብሎ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡ ህላዊ ከዚህ በኋላ የህይወት ዘመን አለቆቹ የህወሃት ሰዎች ቢፈቅዱለት ከነሠራዊት ፍቅሬ፣ ቴዎድሮስ ተሾመ ፣ሙሉአለም ታደሰ…ጋር ፈርሾ የሮማንስ አድቬንቸር ፊልም ስክሪፕት እና ባሩድ ባሩድ የሚሸቱ ግጥሞችን እየጻፈ ማምሻዉን ደግሞ በቀኝ እጁ ቮድካ በግራ እጁ የኮንከር ካርታዉን ታቅፎ በዝምታ ሞቱን ቢጠብቅ አይጠላም፤ ፈቃጅ የለም እንጂ! ከወራት በኋላ በብአዴኑ “ጥረት ኮርፖሬት” የቦርድ አባልነት ዉስጥ አልያም በኢህአዴግ ጽ/ቤት በኩል ብቅ እንደሚል እንጠብቃለን፡፡

የአለቃ ፀጋዬ በርሄ ሹመትና ቀጣይ የቤት ሥራዎች

ጸጋዬ በርሄ

ከስድስተኛ ክፍል ትምህርቱና ከድቁናዉ አቋርጦ 1968ዓም ላይ ደደቢት በረሃ የተገኘዉ የቤተክህነት ሰዉ – ፀጋዬ በርሄ፡፡ ከዓለማዊ ትምህርቱ ይልቅ መንፈሳዊ ትምህርት ላይ የገፋ ሰዉ ነዉ፡፡ አለቃ ጸጋዬ በርሄ ሰባት ዓለማዊ መጽሃፍትን ባያነብም ሰባት ጊዜ ዳዊት ደግሟል፡፡ “አለቃ” የሚለዉ “የማዕረግ” ስሙም ከቤተክህነት ትምህርቱ ጋር ተያይዞ ኮሚኒስት ጓዶቹ ሲያላግጡበት ያወጡለት ስሙ ነዉ፡፡

አለቃ ጸጋዬ በርሄ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ባይጀምርም ዛሬ ላይ በቢዝነስ አድሚስትሬሽን (MBA) የሁለተኛ ዲግሪ “ባለቤት” ነዉ፡፡ ጸጋዬ በርሄ ከትምህርት አኳያ ልክ እንደ ነጭ ወረቀት ንጹህ ነዉ፡፡ ከሴራ ፖለቲካ አኳያ ግን የሚናቅ ሰዉ አይደለም፡፡ እዚህ ላይ መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ አለቃ ጸጋዬ በርሄ የሽማግሌዉ ስብሃት ነጋ ዋርሳ መሆኑ ነዉ፡፡ የስብሃት ነጋ እህት ቅዱሳን ነጋን አግብቷል፡፡ ተንኮሉም ቢሆን ከአምቻ ጋብቻ ዉህድ የተገኘ ይመስላል፡፡ ድንቁርናዉም እንደዛዉ፡፡ ጸጋዬ ላይ የተቀለዱ ቀልዶች ግነት ቢታይባቸዉም ከእዉነታዉ ብዙ የራቁ ግን አይደሉም፡፡ ለአብነት አለቃ ጸጋዬ በርሄ የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት እያለ ዮሃንስ ቤተመንግስት ዉስጥ መለስ በሚመራዉ ስብስባ ላይ ጣልቃ እየገባ ሲያስቸግር መለስ በቁጣ ስሜት “አለቃ ጸጋዬ የስብሰባዉን ህግ ታከብር እንደሆነ አክብር ካልሆነ ግን ይሄን ስብሰባ በእንግሊዝኛ ነዉ የማደርገዉ” ብሎ አሸማቀቀዉ እየተባለ የሚወራዉ ቀልድ የሰዉዬዉን ነጭ ወረቀትነት ለማመላከት ነዉ፡፡

አለቃ ጸጋዬ ህወሓት ረግጦ በሚገዛት ኢትዮጵያ በዋናነት በድሀረ መለስ ከታዩት ፖለቲካዊ አፈናዎች ጀርባ እጁ አለበት፡፡ በመለስ ጊዜም ቢሆን የህወሃት ክፍፍልን ተከትሎ በተፈጠረዉ  የኃይል አሰላለፍ የመለስን ቡድን በመደገፍ የእግረ ረጅሙን ሰዉዬ (ገብሩ አስራት) ወንበር የተረከበ፤ በክልሉ ዉስጥ አኩራፊ እንጂ አንድም ተቃዋሚ እንዳይፈጠር ተግቶ የሰራ፤ የኢዲዩ እና የደርግ ርዝራዥ ናቸዉ ያላቸዉን የትግራይ ሰዎች “ባዶ ስድስት” የተባለ እስር ቤት ያለ ምክንያት በማጎር ያሰቃየ፤ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) መሪ የነበረዉ ፍሰሃ ኃይለማርያምን (ቀደም ሲል የህወሃት ሰዉ ነበር) ኤርትራ በረሃ ላይ በደህንነት ሰዎች ሲገደል ግድያዉን ካቀነባበሩት ግንባር ቀደም ሰዎች አንዱ አለቃ ጸጋዬ በርሄ ነበር፡፡

በድህረ መለሷ ኢትዮጵያ የአለቃ ጸጋዬ ስዉር የአፈና እጆች የከሸፈዉን የአንዳርጋቸዉ ፅጌን የግድያ ሙከራ (ኢሳት በዶክመንተሪ መልክ ሰርቶታል) በማቀነባበር፤ አንድነት ፓርቲን በትእግስቱ አወሉ በኩል እንዲሰነጠቅ በማድረግ፤ ሰማያዊ ፓርቲን በማስተንፈስ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስ ዉስጥ ገብቶ በመፈትፈት፤ መተማ ላይ የተፈናቀሉትን የትግራይ ሰዎች ድራማ በማቀነባበር፤ የወልቃይትን ጉዳይ ይበልጥ በማወሳሰብ ረገድ ሰዉዬዉ እጁ ረጅም ነዉ፡፡ደብረጽዮን የሚያከብረዉ፤ ጌታቸዉ አሰፋ የማይንቀዉ ሰዉ – አለቃ ጸጋዬ በርሄ አሁን ለየት ያለ ተልዕኮ ተሰጥቶታል፡፡

በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ አምባሳደር ተሿሚ ሆኗል፡፡ በዚህ ሹመቱ ህላዊ ዮሴፍ ልቦለድ እያነበበ ያበላሻቸዉን ስራዎች ከኢምባሲዉ ነባር የህወሃት ተሿሚዎች ጋር ሆኖ ማስተካከል ይኖርበታል፡፡

  • ለኤፈርት የንግድ አጋር መሆን የሚችሉ ኩባንያዎችን ማፈላለግ
  • የቤተ እስራኤላዊያንን የከረረ የአንድነት ስሜትና ድጋፍ ማስተንፈስ
  • ሞሳድ ለህወሃት የሚሰጠዉን የደህንነትና ወታደራዊ ስልጠናዎች ሂደት መከታተል የአለቃ ጸጋዬ ተጠባቂ ተልዕኮዎች ናቸዉ፡፡

አለቃ ፀጋዬ ከትግረኛ እና ግዕዝ በመጠኑም ቢሆን ከአማርኛ ቋንቋ በስተቀር ሌላ ቋንቋ ጆሮውን  ቢቆርጡት አይስማም፡፡ የአለቃ ፀጋዬን የቋንቋ ችግር ቀድሞ የተረዳው የጌታቸው አሰፋ የደህንነት መስሪያ ቤት በእስራኤል የኢትዮጵያ ኢምባሲ ውስጥ ከሚሰሩት ሁለት የፖለቲካና ሶስት የደኅንነት አታሼዎች በተጨማሪ ለሁለቱም ዘርፍ ሁለት ሁለት ተጨማሪ ሙያተኞች ከአለቃ ፀጋዬ ጋር ወደ እስራኤል እንዲጓዙ አድርጓል፡፡

ስኳዱን አጠናክሮ የተጓዘው አለቃ ፀጋዬ “ኢኮኖሚውን የሚቆጣጠር ፖለቲካውን ይቆጣጠራል” በሚለው ህወሃታዊ መመሪያ መሠረት ለግዙፉ ኤፈርት የንግድ ኢምፓየር ተጨማሪ ግብአት  ለመፍጠር በቻለው መጠን መትጋቱ ይጠበቃል፡፡ በተለይም በኮንስትራክሽን ዘርፍ (ከሱር ከንስትራክሽን ጋር)፤ በመድኃኒት ምርት (ከአዲስ የመድኃኒት ፋብሪካ ጋር)፤ በእርሻ መሳሪያዎች (ከህይወት ሜካናይዜሽን ጋር) በቴክኖሎጂ ዘርፍ (ከኮምፒዉተር ኔትወርኪንግ ቴክኖሎጅ ሶሉሽን ጋር) እንዲሁም በ“ትዕምት” ስር ካሉ ሌሎች በዝባዥ የንግድ ድርጅቶች ጋር የሚሰሩ የእስራኤል  ባለሀብቶችን በማፈላለጉ ረገድ የአለቃ ፀጋዬ ስኳድ ድርጅታዊ ተልዕኮ ይሆናል፡፡

በእስራኤል የሚኖሩ አብዛኞዎቹ ቤተ እስራኤላዊያን እጅግ ጥብቅ የሆነ የአንድነት ስሜት ያላቸውና የታወቀውሞ ጎራውን የሚደግፉ ናቸው፡፡ ኢሳት በተደጋጋሚ የገቢ ማስባሰቢያ አካሂዶ ከማያፍረባቸው ከተማዎች አንዷ ቴልአቪቭ ነች፡፡ ቤተ እስራኤላዊን በእስራኤል ውስጥ ያላቸው የአንድነት የፍቅር ስሜት ከሌላው አለም ለየት ያለ ነው፡፡ አብዛኞዎቹ ከአንድ አካባቢ (ከጎንደር) የሄዱ በመሆኑ በዘውግ የመከፋፈል ተጋላጭነታቸው ወደ ዜሮ የወረደ ነው፡፡

ቤተ እስራኤላዊያን ከቆይታ ብዛት በወታደራዊ መስክ እስከ መኮንንና የመስመር ኃይል መሪነት የደረሱ፤ በእስራኤል የሀገር ውስጥ የደህንነት መስሪያ ቤት “ሽንቤት” የደህንነት ኦፊሰር የሆኑ፤ በትህምርትና በንግድ የተሳካላቸው፤ በፖለቲካዉ መስክ የካዲማ ፓርቲ አባል በመሆን በእስራኤል  ፓርላማ “ክኔሴት” የፓርላማው ምክትል አፈጉባኤ የሆነውን ሸሎሞ ሞላን ጨምሮ በሊኩድ ፓርቲ በአመራር ደረጃ ቤተ እስራኤላዊያን አሉ፡፡

የጠንካራ ኮሚኒቲ ባለቤት የሆኑት ቤተ እስራኤላዊያን፤ የድህነት ጉዳይ ሆኖ እስራኤል ቢኖሩም ልባቸው ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሆነች በኩራት ይናገራሉ፡፡ ቤተ እስራኤላዊያን ሀገር ቤት ባለው  ጨቋኝና ዘረኛ አገዛዝ ሁሌም እንደተከፉ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ተደጋጋሚ የተቃውሞ ስልፎችን በማዘጋጀትና ለተቃዋሚው ኃይል የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የከረረ ተቃውሟቸዉን በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡

የጥንቱን ሰለሞናዊ ትርከት እንተወውና እስራኤል በአመዛኙ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት የተለሳለሰና ጥቅም ተኮር ነው፡፡ በኃይለሥላሴ ጊዜ ጽዮናዊነነትን አስታክካ ግንኙነቷን በይፋ  የጀመረችው እስራኤል፤ ጽዮናዊነነትን በአደባባይ “ማህበራዊ አደንዛዥ ዕጽ” እያለ ይነቅፍ የነበረው ደርግ ሲመጣም እርሱን ሳትዘልፍ የሽምቅ ተዋጊዎቹንም ሳትደግፍ በተለሳለስ መልኩ መንግሥቱ ኃይለማርያም ያበደበትን “ዘመቻ ሰለሞንን” አሳክታለች፡፡

ህወሓት ማዕከላዊ መንግሥቱን በተቆጣጠረ በወራት ልዩነት ባዘጋጀው የሽግግር መንግሥት ጉባኤ ላይ በተጋባዥነት የፍልስጤሙን ነፃ አውጪ መሪ ያሴር አራፋትን ሲጋብዝ፤ እስራኤል የደንቡን  ያህል ተቃወመች አንጂ አኩርፋ አልቀረችም፡፡ የማታ ማታም የደኅንነት አቅምን ከማሳደግና  የቴክኖሎጂ አቅምን ከማጎልበት አኳያ የሞሳድ ድጋፍ የተገለጠለት ህወሃት ከእስራኤል ጋር በፍቅር ወደቀ፡፡

እስራኤል ለየትኛውም ሀገር በደኅንነትና ወታደራዊ ሥልጠናዎች ዙሪያ ድጋፍ ለመስጠት ቀዳሚ መስፈርቷ ሰብዓዊ መብቶች አለያም ዴሞክራሲያዊ መብቶች የመከበር ያለመከበር ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቁንስ ከተሳካ ታሪካዊ መሰረት ያለው ጽዮናዊነት ካልሆነም ሽብርተኝነትን በተመለከተ ሀገራቱ ያላችውን የአደባባይ አቋምና መልካዊ ምድራዊ አቀማመጥ መገምገም ይቀላታል፡፡

በዚህ ስሌት ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ተመራጭ በተለይም በሶማሊያ ጸረ አሜሪካ-እስራኤል የሆነው አልሸባብ አከርካሪ አለመስበር፤ በኤርትራ ምጽዋ ወደብ ላይ ኢራን፤ ሳውዲ አረቢያና ግብጽ የጦር ቤዝ ለመመስረት ያላቸው ወታደራዊ ፍላጎት፤ የየመናዊያን የርስ በርስ ጦርነት እና ኢራንና የሳውዲ አረቢያ በየመን የውክልና ጦርነት መጀመራቸዉ በዚህ ክፍተት  የሚፈጥረው ኃይል ያሳስባት እስራኤል ኢትዮጵያን አጥብቃ እንድትይዝ አድርጓታል፡፡ መቼም አከራሪ የጽዮን ብሄረተኛው ቤንጃሚን ኔታኒያሁ ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ጉብኝት በጠብታ መስኖ ልማት ዙሪያ ለመፈራረም እንዳልመጣ ግልጽ ነው፡፡

የህወሃት የደህንነት መስሪያ ቤት አቅም ይበልጥ እየፈረጠመ መምጣት ግብአቱ ከአሜሪካና ከእስራኤል የሚሻገር አይደለም፡፡ በተለይም በብርጋዴል ጄኔራል ተክለብርሃን ወልደ አረጋይ የሚመራው የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) የታቀዋሚ ፓርቲ መሪዎችን፣ የጋዜጠኞችን፣ የአክቲቪስቶችን፣ የተጽዕኖ ፈጣሪ አርቲስቶችን እና የታዋቂ ግለሰቦችን የዕለት ተዕለት የስልክ ግንኙነት በመጥለፍ፤ የኢይሜል እና የፌስቡክ አካውንታቸውን በመስበር መረጃዎችን ሲበረብር ውሎ የሚያድርበት የአቅም ምንጭ ከእስራኤል-አሜሪካ የተገኘ ነው፡፡

አለቃ ፀጋዬ፤ ቤተ እስራኤላውያን የአንድነት ኃይሉን የታወቀውሞ ጎራ የሚደግፉበትን ብሄራዊ ስሜት ማስተንፈስ የሚሳካለት ባይመስልም፤ የግዙፉን ኤፈርት የንግድ ኢምፓየር ይበልጥ ለማስፋትና በሞሳድ በኩል ለህወሃት ምልምል የደኅንነት ሰዎች የሚሰጠውን ስልጠና በምልክት ቋንቋ ቢሆን ተደግፎ የሥልጠናውን ሂደት ለመከታተል አይሰንፍም፡፡

የሀገር ቤቱ ህዝባዊ ተቃውሞ አይሎ ህወሓት ወደ መቃብር ቢወርድ እስራኤል አለቃ ፀጋዬን አሳልፋ ባትሰጥም ዴር ሱልጣን ገዳም ውስጥ የብህትውና ህይወት እንዲኖር ፈቃድ የምትነፍገው አትመስልም፡፡ ማን ያውቃል አለቃ ፀጋዬም በአብዮታዊ ዴሞክራሲ የተካውን ዳዊት አንስቶ  ይደግመው ይሆናል፡፡ እስከዚያዉ ግን እስራኤል አንደ መንግሥት ለብሔራዊ ደህንነቷ፤ ህወሃት እንደ ድርጅት ለልዕለ ዘዉግ የበላይነት ወዳጅነታቸው ይቀጥላል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

“አንቱ አጤ ሚኒሊክ ምን ያሉት ሰው ነዎት ?… ” – አሌክስ አብርሃም

$
0
0

የዛሬ አመት በዚህ ወቅት ነው …..አዳራሹ ካፍ እስከገደፉ ግጥም ብሎ በተሰብሳቢወች ተሞልቷል ! የኢሃዴግ ወጣቶች ሊግ ..የሴቶች ሊግ …ጥቃቅንና አነስተኛ ተወካዮች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪ የቀረ የለም ! ለዩኒቨርስቲ ተማሪወች ከሚሰጠው ስልጠና ጎን ለጎን የአገሪቱን ‹‹ነባራዊ ሁኔታ›› ለነዋሪውም ለማስገንዘብ የተዘጋጀ የሶስት ቀን የመወያያ መድረክ ነው … አዳራሹ ዙሪያውን የአክሱም የላሊበላ ምስሎች ተስለውበታል በቀኝ በኩል የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ፎቶ በትልቁ ይታያል በስተግራ የአፄወቹ ምስል ተደርድሯል የአፄ ቴውድሮስ የአፀጼ ሚኒሊክና የአፄ ይኋንስ . . .

ስብሰባው ሶስተኛ ቀኑ ነበር ….ሰብሳቢው እንዳለፉት ሁለት ቀናት ሁሉ ዛሬም እንዲህ ሲል ቀጠለ ‹‹ እና ባለፉት ሁለት ቀናት በስፋት ታሪካችንን እንደዳሰስነው አሁን ላለው የብሄረሰቦች እርስ በእርስ መቃቃር መነሻው አፄ ሚኒሊክ ነበሩ …. አሁን ከኤርትራ ጋር ላለው አንዳንድ ተገቢ ያልሆነ የድንበርና ሌላም ውዝግብም ያው መነሻው የአጼው ስርአት ነበር … ›› እያለ ለድፍን ሶስት ቀናት የአፄ ሚኒሊክን ድክመት ደካማ አስተዳደር እና ፀረ ዴሞክራሲያዊ አገዛዝ ያወገዘበትን ትንታኔ አገባደደ …… ከዛም ህዝቡ ጥያቄ ካለው እንዲያቀርብ እድል ሰጠ!

በስብሰባው ላይ የጥንቱ ሲወገዝ እና ሲገዘት የአሁኑ አገዛዝ የፅድቅ ዘይት ሲቀባና ሲሞካሽ ግራ ከገባቸው ታዳሚወች መካከል አንዲት እናት ከወንበራቸው ተነስተው በቀጥታ ወደሚኒሊክ ፎቶ ሄዱና አዳራሹን በሚያናውጥ ድምፅ ሚኒሊክን በጥያቄ አፋጠጧቸው

‹‹አንቱ አጤ ሚኒሊክ …. አሉ የሚኒሊክ ፎቶ ላይ አፍጥጠው …..እንግዲህ የዚች አገር ችግር ሁሉ መነሻ እርሰዎ ከሆኑ …ጥያቄ አለኝ ለእርሰዎ ! ምን ያሉት ሰው ነዎት ግን ?
ለምንድን ነው ላባችንን ጠብ አድርገን ግብር በምንከፍልበት አገር መብራት በየቀኑ የሚያጠፉብን ?
አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….. ለምንድነው የስልክ ኔትወርኩን የማያስተካክሉልን ‹‹ያለዎት ቀሪ ሂሳብ ›› የምትለው እቴጌ ጣይቱ ናት ?›› ለምን አይመክሩልንም …?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….. የውሃ ማማ በምትባል አገራችን ውሃ እንዲህ የሚያጠፉብን ለምንድን ነው ?
አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….ለምንድነው ልጆቻችን ስራ አጥ እንዲሆኑ ያደረጉብን? ያሰሩብን ”””’

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ””’እርሰዎና ጋሻጃግሬዎቾ በአውቶሞቢል እየፈሰሱ ስለምን ህዝብዎት በትራንስፖርት እጦት ፍዳውን እንዲበላ ፈረዱ ?ማንስ ነው ተጠያቂው?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….ለምንድነው የትምርት ጥራቱ ከእጅ አይሻል ዶማ የሆነው ለምን ልጆቻችንን በነቀዘ ቲወሪ ያነቅዙብናል? ››

አንቱ አጤ ሚኒሊክ …..ለምን ምርጫ በደረሰ ቁጥር አገር ምድሩን ያዋክቡታል ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ …. ለምን ሃሳባቸውን በነፃነት የሚገልፁትን ሁሉ አሸባሪ እያሉ እስር ቤት ይወረውራሉ? ያስደበድባሉ ያስገድላሉ ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….. ለምን የህዝቡን የሰቆቃ ኑሮ በመስተዋት ህንፃወች በቀለበት መንገዶች ግርጌ ሊደብቁ ይፍገመገማሉ ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….. ለምን መርፌ ያነሱ ሙሰኞችን እያሰሩና ከበሮ እያስደቁ በሬ የሚጎትቱትን በዝምታ ያልፋሉ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ …..ለምን በብሔራዊ ቴሌፊዥናችን ብሔራዊ ውሸት ያልኖርነውን ዝባዝንኬ እየተረቱ ያደነቁሩናል ?ለምን ብሔርን ከብሔር የሚያጋጭ የውሸት ታሪክ ይፈጥራሉ ህዝቦችን የሚያቃቅር ሀውልት ያቆማሉ ….ንፁህ ውሃ ያጣ ህዝብ ከጥላቻ ሃውልት ንፁህ ውሃ ይቅዳ ብለው ነው ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ ….. ለምን ፍትሃዊ ምርጫ አይኖርም … እስከመቸ ከዚህ ሁሉ ችግሮዎት ጋር ዙፋንዎት ላይ ይቆያሉ ?
አንቱ አጤ ሚኒሊክ ……እስከመቸ የከበረ ታሪክን በመንደር ቱሪናፋ ሲያራክሱና ዝቅ ሲያደርጉ ይኖራሉ ?

አንቱ አጤ ሚኒሊክ …..እርሰዎ የጀመሩትን እናስቀጥላለን ! በቃ ለመጭዋም ምርጫ እንመርጠዎታለን አሁን ሰብስበው አይነዝንዙን ….ሲሉ እንደእብድ ጮሁ

ሰብሳቢው
‹‹ሴትዮ ….. አካሄድ አካሄድ ……ከአጀንዳ ወጥተዋል›› ሲል ጮኸ
‹‹ አሃ አጀንዳው የሚኒሊክ መስሎኝ …አካሄድ የምትለኝ ታዲያ ወዴት ሂደን እንጩህ .›› ብለው ቀጠሉ ,,,,
አንቱ አጤ ሚኒሊክ ,,,,,,,,,,

Ethiopia: Oppositions Say Dialogue ‘Better Late Than Never’– AllAfrica.com

$
0
0
Photo: Addis Fortune

Putting their differences aside, the ruling and opposition parties have recently come to a round table to find ways of nurturing the political environment for the good of the people.

Using this as a ground, The Ethiopian Herald had approached opposition parties to seek their reflections on the political dialogue.

Unity for Justice and Democracy Party (UJDP) Chairman Tigistu Awolu had this to say: The ruling party seems to have decided to hold the dialogue on various accounts.

For him, the public’s rising concern about the political, economic and social issues has brought the incumbent to a round table with opposition parties.

Tigistu further said formerly, the ruling party did not have a right outlook towards oppositions. “There was a tendency to undermine the role of opposition parties considering them inefficient to hold political power.”

Despite late, the dialogue is crucial for political parties and the government. The track record of other countries tells everyone that parties would come to negotiation table after a series of bloodshed he said, adding that this one is happening without such events in the country.

“I can’t deny the death, imprisonment or migration of our people. But, unlike other countries, we have come to dialogue on our own, without third party involvement as well as further bloodshed.”

Ethiopia Democratic Party (EDP) Central Committee member Gizachew Anemaw for his part said the recent experience in the country has necessitated the dialogue.

EDP understands the importance of discussion, debate and dialogue. These are core principles for peaceful political transformation.

Such political dialogue is not happening in Ethiopian for the first time, Gizachew noted, recalling a ‘similar’ dialogue in 2009. “That dialogue did not bring the desired outcome.”

Gizachew said, change cannot be achieved through violence. In this regard, all facilities have to be in place to carry out peaceful discussions. Enabling environment has to be created. “This is part and parcel of the effort in ensuring human and democratic rights of citizens.”

According to him, the political dialogue is vital to peaceful political transformation and to ease all process towards future democratic elections.

Ethiopian RAEY Party President Teshale Sebro for his part said: “I can’t say the dialogue is timely. It is too late. But, there is still a room for creating better Ethiopia. Had this dialogue taken place some 10 or 15 years ago, we couldn’t have experienced the current bad political situation.”

ክብር ለጀግኖች አባቶቻችን ይሁን እንጂ የትግራይ ባንዳዎችማ ለጣሊያን ባርነት አሳልፈው ሰተውን ነበር፣ – ከ ደረጀ ተፈራ

$
0
0
አጼ ዮሐንስ 4ኛ ከሞቱ በኋላ ልጆቻቸው አባታቸው ከእንግሊዝ ጋር በገቡት የሂወት ውል ምጽዋ ላይ እንግሊዞች የተከሉትን ጣሊያን የሚባል ወራሪ እንደ መንቀል ትኩረታቸው ጥቅምና ስልጣን ላይ ሆነ። ዮሐንስ ከእንግሊዝ ጋር በመመሳጠር ለአጼ ቴዎድሮስ ሞት ምክንያት እንደሆኑ ሁሉ ልጆቻቸውም በተራቸው ከጣሊያን ጋር በሚስጥር በመደራደር (Treaty በመፈራረም) ምኒሊክን አስገድለው ለመንገስ ይዶልቱ ነበር።
በልጅ ያልታደሉት አጼ ዮሐንስ የፓለቲካ ብስለት ይጉደላቸው፣ ግራ ቀኙን የማያስተውሉ ጀብደኛ ይሁኑ እንጂ በተዋጊነት አይታሙም። ልጆቻቸው ግን ከምንም ውስጥ የሌሉ ከንቱዎች ነበሩ። የሚገርመው ከአባታቸው ብሰው ለፈረንጅ በእጥፍ አጎብዳጅ ሆኑ። ሁሉን ነገር ትተውት ዋናው ዓላማቸው ከጣሊያን ጋር አብረን ምኒልክን አስወግደን ስልጣን እንያዝ የሚል ብቻ ሆነ። በመሆኑና ምኒልክ ይህን ተናገረ ይህን ሊያደርግ ነው በሚል የአሉባልታ ወሬ ተጠመዱ። ራስ መንገሻ ዮሐንስ ከአድዋ ጦርነት በፊት ኢትዮጵያን ከድተው እጃቸውን ለጣሊያን ሰተው ነበር ነገር ግን ከጣሊያኖች የሚፈልጉትን ማግኘት ስላልቻሉ ተመልሰው በመምጣት አጼ ምኒልክን ይቅርታ ጠየቁ። በይቅርታ የሚያምኑት ደጉ ንጉስ ምኒሊክም ይቅርታ አደረጉላቸው። በአድዋው ጦርነት ከጠላት ወገን ነው የመጣው ብለው ሳይጠራጠሯቸው በአድዋው ጦርነት ላይ እንዲሳተፉ አደረጓቸው። “ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይተውም” እንደሚባለው ከአድዋ ጦርነት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ንጉሱን ከድተው ሸፈቱ ይሁንና ንጉሱ ማርከው በማምጣት (መግደል ሲችሉ) በሸዋ አንኮበር የቁም እስረኛ አድርገው አስቀመጧቸው። ባጠቃላይ እነ ራስ መንገሻ ዮሐንስ በውትድርናውም ሆነ በዲፕሎማሲው ምንም ዓይነት ብቃት ያልነበራቸውም፣ በነገር (conspiracy) የተካኑ  ከንቱ ፍጥረት ነበሩ።
ዮሐንስ ልጆች ለጣሊያንና ለእንግሊዝ የነበራቸውን አጎብዳጅነት ከእነሱም አልፎ ወደ አሽከሮቻቸውና ወደ ተራው የትሬ ህዝብ እንደ ጉንፋን በሽታ በመተላለፉ በአድዋ ጦርነት ወቅት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የትግሬ ቅጥረኛ ወታደሮች መፈጠር ቻሉ። በመሆኑም ጣሊያኖች ኢትዮጵያን ሲወሩ በርካታ ቅጥረኛ የትግሬ ተዋጊዎችን (Askaris) ከጎናቸው አሰልፈው በኢትዮጵያ አርበኞች ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት ማድረሳቸውን ታሪክ ይነግረናል።
የባንዳ ልጅ ባንዳ ነውና ይህ ለፈረንጅ ማጎብደድ በዘር እንደሚተላለፍ ተላላፊ ደዌ ከአባት ወደ ልጅ ሲተላለፍ ቆይቶ የአድዋ ጦርነት ከተደረገ ከ40 ዓመት በኋላ የአጼ ዮሐንስ የልጅ ልጅ የሆነው ኃ/ስላሴ ጉግሳ 20ሺህ በስሩ የነበሩትን ወታደሮች ይዞ ለጣሊያን እጁን ሰጠ (ገባ)። እጁን በመስጠት ሳያበቃ በርካታ የትግሬ መሳፍንትን ወደ ጣሊያን እንዲኮበልሉ በማድረግና የኢትዮጵያን አርበኞች በመውጋቱ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል።
አሁን ባለንበት ዓለም በሰለጠነበት ጊዜ ወደ ኋላ ሄደው ቀኝ ገዢዎች አፍሪካን ለመግዛት ይጠቀሙበት የነበረውን የከፋፍለህ ግዛ ፓሊሲያቸው ማስፈጸሚያ ስልት ሆኖ ሲያገለግላቸው የነበረውን Tribalism Politics  የጣሊያን ባንዳ ልጆች የሆኑት ወያኔ ትግሬዎች በብሔር ብሔረሰብ ስም እንደ አሜባ ቅርጻቸውን ቀይረው በመምጣት ጣሊያንንና ባንዳ አባቶቻቸውን አነባብሮ የመታውን የኢትዮጵያን ህዝብ እርስ በርሱ በማጋጨት ቂማቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።
ከፋሽስት ጣሊያን ጎን ተሰልፈው አርበኞቻችንን ሲገሉ የነበሩት የባንዳ ልጆች ዛሬ በለስ ቀንቷቸው ስልጣን ቢይዙ ጀግኖች አባቶቻችን የተሰውለትን ሰንደቅ አላማ ጨርቅ ነው፣ አክሱም ለወላይታው ምኑ ነው በማለትና፣ የኢትዮጵን ታሪክ የሚጀምረው ጣሊያን ከተሸነፈበት ከአድዋ ድል በኋላ እንደሆነ ያህል በመቶ አመት ገድበውና የሃገራችንን ታሪክ በማጠልሸት፣ የጥቁር ህዝብ ኩራት የሆኑትን ታላቁን የአድዋውን ጀግና ንጉስ አጼ ምኒልክንና ከእሳቸው ጎን የዘመቱትን ስም ጥር ጀግኖቻችንን በፈጠራ ወሬ ስማቸውን በማጥፋት ላይ ይገኛሉ። ይህ የሚያሳየው ወያኔና ደጋፊዎቹ በዘር የተላለፈ የማይለቅ በባንዳነት ደዌ የተለከፉ ድኩማን መሆናቸውን ነው።
ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች አባቶቻችን ይሁንና የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የጉራጌ፣ የሃድያ፣ የሲዳማ፣ የከንባታ፣ ባጠቃላይ ከመላው የሃገራችን ክፍል የዘመቱ አርበኛ አባቶቻችን የሃገራችንን አረንጎዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ አላማ አንግበው በዱር በገደሉ በ5ቱ የአርበኞች የትግል ዓመታት ተንከራተው ነጻ ባያወጡን ኖሮ ትግሬዎችማ ለጣሊያን ባርነት አሳልፈው ሰተውን ነበር።
ክብር ለጀግኖች አባቶቻችን!
አሜን!
Viewing all 3686 articles
Browse latest View live